ፌስቡክ የዶናልድ ትራምፕን ድምጽ ከገጹ ላይ አገደ

ዶናልድ ትራምፕ

የፎቶው ባለመብት, EPA

ፌስቡክ የአሜሪካው የቀድሞ ፕሬዝዳንት የዶናልድ ትራምፕ ተንቀሳቃሽ ምስልን ከልጃቸው ሚስት ላራ ትራምፕ ገጽ ላይ አወረደ።

ግዙፉ የማኅበራዊ ሚዲያ ተቋም የትራምፕን ምስል ከገጹ ላይ ያነሳው በታኅሣሥ ወር ላይ ነውጠኛ ደጋፊዎቻቸው ዋሺንግተን የሚገኘውን ካፒቶል ሒል ህንጻ ካጠቁ በኋላ ነበር።

ላራ ትራምፕ ፎክስ ኒውስ ላይ አልፎ አልፎ የምትቀርብ ሲሆን አማቿ የሆኑትን ትራምፕን በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ቃለመጠይቅ አድርጋላቸው ነበር።

በኋላ ላይም ፌስቡክ በኢሜል አድራሻዋ የጻፈላትንና ልትታገድ እንደምትችል የሚገልጸውን መልዕክት ፎቶ አንስታ አጋርታለች።

"ዶናልድ ትራምፕን ከፌስቡክ እና ከኢንስታግራም ለማገድ ባስቀመጥነው መመሪያ መሰረት የዶናልድ ትራምፕን ድምጽ የያዘ መልዕክት ወዲያውኑ ይነሳል፤ በተጨማሪም በአካውንቱ ላይ ተጨማሪ እቀባ ይደረጋል" ይላል በካትሊን የተጻፈው ይህ ኢሜል።

የ Instagram ይዘትን ይለፉት
ይዘቱን Instagram ይፈቅዳሉ?

ይህ ጽሑፍ በInstagram. የቀረበ ይዘት ይዟል። ገጹ ቴክኖሎጂዎች ወይም ኩኪዎች ሊኖረው ስለሚችል ገጹ ከመከፈቱ በፊት የእርስዎን ፍቃድ እንጠይቃለን። ፍቃድዎን ከመስጠትዎ በፊት የInstagram ኩኪ ፖሊሲ እና የ ማንበብ ይፈልጉ ይሆናል። ይዘቱን ለማንበብ ‘እቀበላለሁ ቀጥል’ የሚለውን ይምረጡ።

ማሳሰቢያ፡ የሦስተኛ ወገን ይዘቶች ማስታወቂያ ሊኖራቸው ይችላል

የ Instagram ይዘት መጨረሻ

የዶናልድ ትራምፕን ልጅ ኤሪክ ትራምፕን ያገባችው፤ ላራ ትራምፕ በኢንተርኔት ላይ በሚቀርበው የራሷ ፕሮግራም ከዶናልድ ትራምፕ ጋር ያደረገችውን ቆይታ በቀጥታ ከመጫን ይልቅ ማስፈንጠሪያውን በገጿ ላይ አስቀምጣ ነበር።

ፌስቡክ ትራምፕን ከገጹ ላይ ያገዳቸው በፈረንጆቹ ታኅሣሥ 7/2020 ነውጠኛ ደጋፊዎቻቸው የአሜሪካ ምክር ቤት መቀመጫ የሆነውን የካፒቶል ሒል ህንጻን ከወረሩና ጥቃት ከፈጸሙ በኋላ ነው።

በወቅቱ ማርክ ዙከርበርግ ውሳኔውን በተመለከተ ሲናገር "ፕሬዝዳንቱ በዚህ ወቅት የእኛን አገልግሎት እንዲጠቀሙ መፍቀድ ያለው አደጋ ከፍተኛ መሆኑን እናውቃለን" ብሎ ነበር።

ዶናልድ ትራምፕ ከትዊተር እና ከዩቲዩብም መታገዳቸው ይታወሳል።