ስሪ ላንካ በመንትያ ቁጥር ክብረ ወሰን ለመስበር ያደረገችው ሙከራ ከሸፈ

የፎቶው ባለመብት, AFP
ስሪ ላንካ በመንትያ ቁጥር ክብረ ወሰን ለመስበር ያደረገችው ሙከራ ሳይሳካላት ቀርቷል።
በሲሪ ላንካ የሚገኙ መንተዮች በሙሉ በመዲናዋ ኮሎምቦ በአንድ ስታዲየም ውስጥ እነዲሰባሰቡ ጥሪ ተደርጎላቸው ነበር። ዓላማውም በፈረንጆቹ 1999 ላይ በታይዋን ተይዞ የነበረውን የዓለም ክብረ ወሰን ለመስበር ነበር።
ታይዋን 3 ሺ 961 መንትያዎችን፣ 37 በአንዴ ሦስት ሆነው የተወለዱ መንትያዎች እንዲሁም 4 ሆነው የተወለዱ አራት መንትያዎችን በአንድ ስፍራ በማሰባሰብ በዓለም የድንቃ ድንቅ መንዘገብ ላይ ተመዝግባ ትገኛለች።
ሰሪ ላንካውያኑ በርካታ መንትያዎችን በአደባባይ ጠርተው ለዕይታ ቢያበቁም በታይዋን የተያዘውን ሪኮርድ ግን መስበር አልተቻላቸውም።
ጥሪውን ተከትሎ ከተጠበቀው በላይ ቁጥራቸው ከፍተኛ የሆነ መንትዮች ተገኝተዋል። ታዲያ የዓለም ድንቃ ድንቅ መዝገብ መስፍርቶችን ለማሟላት እና የልደት የምስክር ወረቀቶችን ለማረጋገጥ በቂ ጊዜ ማግኘት አልተቻለም።

የፎቶው ባለመብት, AFP
መንትዮቹ የተሰባሰቡት አገራቸውን በዓለም ክብረወስን ለማስመዝገብ ነበር።

የፎቶው ባለመብት, Reuters

የፎቶው ባለመብት, Reuters
አዘጋጆቹ 5 ሺህ መንትያዎችን በመመዝገብ ክብረወሰኑን ለመስበር ግብ አስቀምጠው ነበር።

የፎቶው ባለመብት, Reuters
ኤኤፍፒ እንደዘገበው ከሆነ ግን 14 ሺህ ሰዎች በማስታወቂያው መሰረት ለዝግጅቱ ተመዝግበው ነበር።

የፎቶው ባለመብት, AFP

የፎቶው ባለመብት, EPA

የፎቶው ባለመብት, Reuters
መንትዮቹም በድጋሜ መጥተው ለመመዝገብና በታይዋን ተይዞ የሚገኘውን ክብረወሰን ለመስበር ሁሌም ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።














