ስሪ ላንካ በመንትያ ቁጥር ክብረ ወሰን ለመስበር ያደረገችው ሙከራ ከሸፈ

ስሪ ላንካ በመንትያ ቁጥር ክብረ ወሰን ለመስበር ያደረገችው ሙከራ ሳይሳካላት ቀርቷል።

በሲሪ ላንካ የሚገኙ መንተዮች በሙሉ በመዲናዋ ኮሎምቦ በአንድ ስታዲየም ውስጥ እነዲሰባሰቡ ጥሪ ተደርጎላቸው ነበር። ዓላማውም በፈረንጆቹ 1999 ላይ በታይዋን ተይዞ የነበረውን የዓለም ክብረ ወሰን ለመስበር ነበር።

ታይዋን 3 ሺ 961 መንትያዎችን፣ 37 በአንዴ ሦስት ሆነው የተወለዱ መንትያዎች እንዲሁም 4 ሆነው የተወለዱ አራት መንትያዎችን በአንድ ስፍራ በማሰባሰብ በዓለም የድንቃ ድንቅ መንዘገብ ላይ ተመዝግባ ትገኛለች።

ሰሪ ላንካውያኑ በርካታ መንትያዎችን በአደባባይ ጠርተው ለዕይታ ቢያበቁም በታይዋን የተያዘውን ሪኮርድ ግን መስበር አልተቻላቸውም።

ጥሪውን ተከትሎ ከተጠበቀው በላይ ቁጥራቸው ከፍተኛ የሆነ መንትዮች ተገኝተዋል። ታዲያ የዓለም ድንቃ ድንቅ መዝገብ መስፍርቶችን ለማሟላት እና የልደት የምስክር ወረቀቶችን ለማረጋገጥ በቂ ጊዜ ማግኘት አልተቻለም።

መንትዮቹ የተሰባሰቡት አገራቸውን በዓለም ክብረወስን ለማስመዝገብ ነበር።

አዘጋጆቹ 5 ሺህ መንትያዎችን በመመዝገብ ክብረወሰኑን ለመስበር ግብ አስቀምጠው ነበር።

ኤኤፍፒ እንደዘገበው ከሆነ ግን 14 ሺህ ሰዎች በማስታወቂያው መሰረት ለዝግጅቱ ተመዝግበው ነበር።

መንትዮቹም በድጋሜ መጥተው ለመመዝገብና በታይዋን ተይዞ የሚገኘውን ክብረወሰን ለመስበር ሁሌም ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።