ኮሮናቫይረስ፡ህንድ በአዲሱ የክትባት ፖሊሲዋ በአንድ ቀን 8 ሚሊዮን ሰው ከተበች

የፎቶው ባለመብት, Getty Images
ህንድ ይፋ ባደረገችው አዲስ የ ኮቪድ ክትባት ፕሮግራም የመጀመሪያ ቀን ብቻ ስምንት ሚሊዮን ሰዎችን በመከተብ ሪኮርድ አሰመዝግባለች፡፡
በአዲሱ ፖሊሲ መሰረትም የፌዴራል መንግስት የኮቪድ -19 ክትባቶችን ከአምራቾች በመግዛት እና ለክልሎች እያቀረበ ይገኛል፡፡
ህንድ በዓለም ላይ ካሉ ግዙፍ የክትባት አምራች አገራት መካከል ብትሆንም የራሷን ዜጎች የምትከትብበት ፍጥነት ግን እጅግ ዝቅተኛ የሚባል ነበር፡፡
እስከአሁንም ባጠቃላይ ለክትባቱ ብቁ ተብለው ከተለዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ውስጥ አምስት በመቶውን ብቻ ሙሉ በሙሉ መከተብ የቻለች ሲሆን እጥረቶችም በበርካታ ክልሎች እየታዩ ነው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ ሁሉም ሰው ከሰኔ 21 ጀምሮ "ነፃ ክትባት" ያገኛል ብለው ነበር፡፡
አዲሱ ክትባት ፖሊሲ በተተገበረበት የመጀመሪያ ቀንም የአገሪቱን ክትባት መርሃግብር ፍጥነትን አድንቀዋል፡፡
በቀድሞው የኮቪድ ክትባት ፖሊሲ መሠረት በሕንድ ውስጥ ከሚመረቱት ክትባቶች ውስጥ ግማሹ ወደ ፌዴራል መንግሥት ያቀኑ ሲሆን የተቀሩት ደግሞ ወደ ክልል አስተዳደሮችና ወደ የግል ሆስፒታሎች ይላካሉ ፡፡
ምንም እንኳን ክልሎች ከ 18-44 ዓመት የእድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ሰዎችን ለመከተብ በመደበኛ የገበያ ውድድር ተፈትነው ክትባቱን ቢገዙም ተከታቢዎች ግን ክትባቱን በነፃ ያገኛሉ፡፡
በተመሳሳይ የፌዴራል መንግሥቱም ለተጋላጭ ሰራተኞች እና ከ 45 ዓመት በላይ ለሆኑ ሰዎች ክትባቱን እንዲሁ በነጻ ይሰጣል፡፡
በአዲሱ ፖሊሲ የፌዴራል መንግስት አሁን ከተመረቱት ክትባቶች ሁሉ 75% ይገዛል ፡፡
የክልል መንግስታት በቀጥታ ከአምራቾች ጋር ከመደራደር ይልቅ የክትባት ክትባቶቻቸውን ከፌዴራል መንግስት በነፃ ይቀበላሉ ፡፡
ሆኖም ቀሪዎቹ 25% ክትባቶች አሁንም እንደበፊቱ በግል ሆስፒታሎች ግዥ እንዲከናወኑ መደረጉን ልብ ማለት ይገባል ፡፡
እነዚህ ክትባቶች ነፃ አይደሉም - እና በግል ሆስፒታሎች መከፈል አለባቸው ፡፡
በአዲሱ ፖሊስ ግን የፌደራል መንግስት ከሚመረተው ክትባት ውስጥ 75 በመቶውን የሚገዛ ይሆናል፡፡ የክልል በተናጠል ተደራድረው ከመግዛት ይልቅ መንግስታትም ክትባቶቻቸውን ከፌደራሉ መንግስት በነፃ ይቀበላሉ፡፡
ነገር ግን አሁንም 25 በመቶው የክትባት ምርት የግል ሆስፒታሎች እንዲገዙት የሚተው ሲሆን በእነዚህ ተቋማት ክትባቱ በክፍያ እየሰጡ ይቀጥላሉ፡፡












