"አሜሪካ ምኞቷ ሞላላት"፡ ዶናልድ ትራምፕ

የፎቶው ባለመብት, Reuters
የአሜሪካው ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ከሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን ጋር ያደሩጉትን ውይይት "እምነት የተሞላበት ፣ቀጥተኛና ውጤታማ ነበር" ሲሉ አሞካሹት።
በስምምነቱ አሜሪካ ከሰሜን ኮሪያ ጋር ያላትን የጦር መሳሪያ ፉክክር ለማቆም እንዲሁም ሰሜን ኮሪያም የሚሳይል ሙከራ የምታደርግበትን ክልል ለማጥፋት ቃል ገብተዋል።
የኮሪያን ሰርጥ ከኑክሌር መሳሪያ ነፃ ማድረግም በስምምነታቸው ውስጥ ተካቷል።
በሰብዓዊ መብት ዙሪያ በተለይም ዜጎችን በግዞት መልክ የሚደረግን የጉልበት ብዝበዛን አስመልክተው ጉዳዩን ከኪም ጋር በነበራቸው የሁለትዮሽ ውይይት አንስተዋል።
ኪም የኮሪያን ሰርጥ ከኑክሌር ነፃ ለማድረግ እንደማያመነቱ በንግግራቸው አረጋግጠዋል፤ ይህ ጉዳይ አሜሪካም አጥብቃ ስትሻው የነበረው ነው።
ሁለቱ አገራት ወደፊት ለሚመሰርቱት አዲስ ግንኙነት እንደሚተባበሩና አሜሪካም ለሰሜን ኮሪያ የደህንነት ዋስትና እሰጣለሁ ብላለች።
የአሜሪካ ተቀማጭ ፕሬዚዳንትና የሰሜን ኮሪያው መሪ ሲገናኙ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ።










