ሕንድ ውቅያኖስ ውስጥ የገባው መኪና እየተፈለገ ነው

የሰውና የእቃ ማሻገሪያ መርከብ

የፎቶው ባለመብት, Twahir H.Kassim

ከኬንያ ሞምባሳ ወደብ ወደ ባህር ዳርቻው የእቃና የሰው ማሻገሪያ መርከብ ላይ ሆኖ ሲያቋርጥ የነበረ መኪና ሕንድ ውቅያኖስ ውስጥ ገብቶ እየተፈለገ መሆኑ ተገለፀ።

መኪናው ውስጥ ሦስት ሰዎች ሳይኖሩ እንዳልቀረ የኬንያ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

አደጋው ትናንት ያጋጠመ ሲሆን ከሞምባሳን ወደ ሊኮኒን በማቋረጥ ላይ ሳለ መሃል ላይ ሲደርስ ወደ ኋላ በመንሸራተቱ አደጋው እንዳጋጠመው ታውቋል።

አደጋው ሲደርስ የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምስልም በትዊትር ላይ በስፋት ተሰራጭቷል።

የ X ይዘትን ይለፉት
ይዘቱን X ይፈቅዳሉ?

ይህ ጽሑፍ በX. የቀረበ ይዘት ይዟል። ገጹ ቴክኖሎጂዎች ወይም ኩኪዎች ሊኖረው ስለሚችል ገጹ ከመከፈቱ በፊት የእርስዎን ፍቃድ እንጠይቃለን። ፍቃድዎን ከመስጠትዎ በፊት የX ኩኪ ፖሊሲ እና የ ማንበብ ይፈልጉ ይሆናል። ይዘቱን ለማንበብ ‘እቀበላለሁ ቀጥል’ የሚለውን ይምረጡ።

ማሳሰቢያ፡ የሦስተኛ ወገን ይዘቶች ማስታወቂያ ሊኖራቸው ይችላል

የ X ይዘት መጨረሻ

የዓይን እማኞች ለዴይሊ ኔሽን ጋዜጣ እንደተናገሩት እንዲት ሴትና ሕፃን መኪናው ውስጥ ነበሩ።

"አንዲት ሴትና ወንድ ልጅ መኪናው ውስጥ ሆነው ተመልክቻለሁ፤ መኪናው ሲገለበጥ ሴትዮዋ ስትጮህና እርዳታ ስትጠይቅ ነበር። ከዚያም የነፍስ አድን ሠራተኞችን እንዲደርሱላቸው ላኩላቸው" ብለዋል።

ዴይሊ ኔሽን ፖሊስን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው በመኪናው ውስጥ የነበሩ ሰዎች ቁጥር አራት ነው።

የኬንያ የመርከብ አገልግሎት ባለሥልጣን ፍለጋውና የነፍስ አድን ሥራው እንደቀጠለ አስታውቋል።

የሰው እና ዕቃ ማሻገሪያ መርከቡ ኦፕሬተር እስካሁን በፍለጋው ምንም ፍንጭ አለመገኘቱን በትዊተር ገፃቸው አስታውቀዋል።