የዓለም መሪዎች ስለዳግማዊት ንግሥት ኤልዛቤጥ ምን እያሉ ነው?

የፎቶው ባለመብት, Getty Images
የዓለም መሪዎች እና ታላላቅ ሰዎች በ96 ዓመታቸው ባረፉት ንግሥት ኤልዛቤጥ ሞት የተሰማቸውን ሐዘን እየገለጹ ነው።
በዚህም ንግሥቲቱ በነበራቸው ኃላፊነትን የመወጣት ብቃትና ጽናት እንዲሁም መልካምነታቸውን በመጥቀስ ሐዘናቸውን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በንግሥት ኤልዛቤጥ ሞት የተሰማቸውን ሐዘን በትዊተር ገጻቸው ላይ አስፍረተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እንዳሉት፣ በኢትዮጵያም መንግሥት እና ሕዝብ ስም “በግርማዊት ዳግማዊት ንግሥት ኤልዛቤጥ ሞት የተሰማኝን ጥልቅ ሐዘን፤ ለብሪታኒያ ንጉሣዊ ቤተሰብ፣ መንግሥት እና ሕዝብ” አገልጻለሁ ብለዋል።
ይህ ጽሑፍ በX. የቀረበ ይዘት ይዟል። ገጹ ቴክኖሎጂዎች ወይም ኩኪዎች ሊኖረው ስለሚችል ገጹ ከመከፈቱ በፊት የእርስዎን ፍቃድ እንጠይቃለን። ፍቃድዎን ከመስጠትዎ በፊት የX ኩኪ ፖሊሲ እና የ ማንበብ ይፈልጉ ይሆናል። ይዘቱን ለማንበብ ‘እቀበላለሁ ቀጥል’ የሚለውን ይምረጡ።
የ X ይዘት መጨረሻ
የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን “የፈረንሳይ ወዳጅ” በማለት የገለጿቸው ንግሥቲቷ “ቀና ልብ ያላቸው” ብለዋቸዋል።
የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ ንግሥቲቱ በነበራቸው ብቃትና “ባልደከመ የሥራ ሥነ ምግባር” ዓለምን ማርከው ነበር።

የፎቶው ባለመብት, 10 DOWNING STREET
ንግሥቲቱን በመጀመሪያ ከ40 ዓመታት በፊት አግኝተዋቸው የነበሩትና ባለፈው ዓመት በተገናኙበት ጊዜ አስደሳች አቀባበል ያደረጉላቸው የአሁኑ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ደግሞ፣ “ከንግሥትም በላይ ነበሩ፣ የኖሩበት ዘመን መገለጫ ነበሩ” በማለት አድናቆታቸውን ገልጸዋል።
ዳግማዊት ንግሥት ኤልዛቤጥ በንግሥና ዘመናቸው 13 የአሜሪካ ፕሬዝዳንቶችን አግኝተዋል።

የፎቶው ባለመብት, Getty Images
ዶናልድ ትራምፕም “የግርማዊነታቸውን መልካም ወዳጅነትን፣ ታላቅ ጥበብን አስደናቂ ቀልድ አዋቂነታቸውን ፈጽሞ አልረሳውም” ብለዋል።
“ታላቅ እና ውብ ሴት ነበሩ፣ እሳቸውን የሚመስል ማንም ሰው አልነበረም” በማለት ትራምፕ በራሳቸው የማኅበራዊ ሚዲያ መድረክ ላይ ሐዘናቸውን አስፍረዋል።
ሌላኛው የአሜሪካ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጆርጅ ወደብሊው ቡሽም ከንግሥቲቱ ጋር ሻይ የጠጡበትን ጊዜ በማስታወስ ለዳግማዊት ኤልዛቤት ያላቸውን አድናቆት ገልጿል።

የፎቶው ባለመብት, Getty Images
ርዕሰ ብሔሯ የነበሩት ካናዳ በንግሥቲቱ የሥልጣን ዘመን ውስጥ 12 ጠቅላይ ሚኒስትሮች ተፈራርቀውባታል።
በእጅጉ ያዘኑት ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ንግሥቲቱ ለካናዳውያን “በግልጽ የሚታይ ጥልቅ እና ታማኝ ፍቅር ነበራቸው።”
በተጨማሪም ከአፍሪካ የኬንያው ተመራጭ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ፣ የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ፤ ከእስያ ደግሞ የታላላቆቹ አገራት የቻይና እና የሕንድ መሪዎች በንግሥቲቱ ሞት የተሰማቸውን ሐዘን ገልጸዋል።
በሌሎች በዓለም ዙሪያ ያሉ የአገራት መሪዎች እና ታላላቅ ሰዎች በዳግማዊት ንግሥት ኤልዛቤት ሞት ሐዘናቸውን ለንጉሣውያኑ ቤተሰብ፣ ለታላቋ ብሪታኒያ መንግሥት እና ሕዝብ የሐዘን መግለጫ እያስተላለፉ ነው።












