አውሮጳውያን ክርስትያኖች አጥንት በሚቆረጥም ብርድ የጥምቀት በዓል እያከበሩ ነው

ጥምቀት በአውሮጳ

የፎቶው ባለመብት, Reuters

የምስሉ መግለጫ, ጥምቀት በአውሮጳ

የኦርቶዶክስ ክርስትና ዕምነት ተከታዮች የጥምቀት በዓልን ለማክበር በረዶ በሰራ ውሃ ውስጥ እየተጠመቁ ነው።

በኦርቶዶክስ አማኞች ዘንድ ከፍተኛ ቦታ ከሚሰጣቸው በዓላት መካከል አንዱ የሆነው የጥምቀት በዓል በሩሲያና በምስራቅ አውሮጳ አገራት በስፋት ይከበራል።

በዓሉ በየዓመቱ በአውሮፓውያኑ አቆታጠር ጥር 19 ይከበራል።

ጥምቀት በአውሮጳ

የፎቶው ባለመብት, Reuters

የምስሉ መግለጫ, ጥምቀት በአውሮጳ

በዓሉን ለማክበር በርካታ የኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ራሳቸውን በረዶ በሰራ የውሃ ጉድጓድ ውስጥ ይከታሉ። ውሃው ውስጥም ሶስቱን ስላሴዎች ለማሰብ ሦስት ጊዜ ይጠልቃሉ።

ጥምቀት በአውሮጳ

የፎቶው ባለመብት, Reuters

ይህች ሴት የሙቀት መጠኑ ከዜሮ በታች 10 ዲግሪ ሴንቲ ግሬድ በሆነበት ቅዝቃዜ ውስጥ ሩሲያ ኦምስክ በምትባል ከተማ ውስጥ የጥምቀት ሥነ ስርዓትን እያከናወነች ነው።

ጥምቀት በአውሮጳ

የፎቶው ባለመብት, AFP

ጥምቀቱም ጤናን በማስፈንና ሃጢያትን ያስተሰርያል ተብሎ ይታመናል። ከላይ ያለው ምስል የሚያሳየው በሩሲያ መዲና ሞስኮ ዳርቻ አካባቢ ስቭያቶዬ በተባለ ስፍራ አንድ የኦርቶዶክስ ቄስ ውሃውን ሲባርኩት የሚያሳይ ነው።

ጥምቀት በአውሮጳ

የፎቶው ባለመብት, AFP

አማኞች እንደሚሉት የጥምቀት ዕለት ሁሉም ውሃ ቅዱስ ይሆናል። በሌላ በኩል አንዳንዶቹ የቀዘቀዘው ውሃ ለጤና ጠቃሚ ነው ይላሉ። ከላይ የምንመለከታቸው ምዕመናን ከጥምቀት በኋላ ለፎቶ ተሰባስበው ነው።

እምቀት በአውሮጳ

የፎቶው ባለመብት, Reuters

እነዚህ እስረኞች በኦምስክ በከፍተኛ ጥበቃ ውስጥ ሆነው ለጥምቀቱ እራሳቸውን ወደ ጥልቁ የውሃ ጉድጓድ ሲወረውሩ የእስር ቤቱ ጠባቂዎች እየተመለከቱ ነው።