አውሮጳውያን ክርስትያኖች አጥንት በሚቆረጥም ብርድ የጥምቀት በዓል እያከበሩ ነው

የፎቶው ባለመብት, Reuters
የኦርቶዶክስ ክርስትና ዕምነት ተከታዮች የጥምቀት በዓልን ለማክበር በረዶ በሰራ ውሃ ውስጥ እየተጠመቁ ነው።
በኦርቶዶክስ አማኞች ዘንድ ከፍተኛ ቦታ ከሚሰጣቸው በዓላት መካከል አንዱ የሆነው የጥምቀት በዓል በሩሲያና በምስራቅ አውሮጳ አገራት በስፋት ይከበራል።
በዓሉ በየዓመቱ በአውሮፓውያኑ አቆታጠር ጥር 19 ይከበራል።

የፎቶው ባለመብት, Reuters
በዓሉን ለማክበር በርካታ የኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ራሳቸውን በረዶ በሰራ የውሃ ጉድጓድ ውስጥ ይከታሉ። ውሃው ውስጥም ሶስቱን ስላሴዎች ለማሰብ ሦስት ጊዜ ይጠልቃሉ።

የፎቶው ባለመብት, Reuters
ይህች ሴት የሙቀት መጠኑ ከዜሮ በታች 10 ዲግሪ ሴንቲ ግሬድ በሆነበት ቅዝቃዜ ውስጥ ሩሲያ ኦምስክ በምትባል ከተማ ውስጥ የጥምቀት ሥነ ስርዓትን እያከናወነች ነው።

የፎቶው ባለመብት, AFP
ጥምቀቱም ጤናን በማስፈንና ሃጢያትን ያስተሰርያል ተብሎ ይታመናል። ከላይ ያለው ምስል የሚያሳየው በሩሲያ መዲና ሞስኮ ዳርቻ አካባቢ ስቭያቶዬ በተባለ ስፍራ አንድ የኦርቶዶክስ ቄስ ውሃውን ሲባርኩት የሚያሳይ ነው።

የፎቶው ባለመብት, AFP
አማኞች እንደሚሉት የጥምቀት ዕለት ሁሉም ውሃ ቅዱስ ይሆናል። በሌላ በኩል አንዳንዶቹ የቀዘቀዘው ውሃ ለጤና ጠቃሚ ነው ይላሉ። ከላይ የምንመለከታቸው ምዕመናን ከጥምቀት በኋላ ለፎቶ ተሰባስበው ነው።

የፎቶው ባለመብት, Reuters
እነዚህ እስረኞች በኦምስክ በከፍተኛ ጥበቃ ውስጥ ሆነው ለጥምቀቱ እራሳቸውን ወደ ጥልቁ የውሃ ጉድጓድ ሲወረውሩ የእስር ቤቱ ጠባቂዎች እየተመለከቱ ነው።












