ፍራቻና ኃዘን የተቀላቀለበት የእስራኤል-ጋዛ ሁኔታ በፎቶዎች

በእስራኤል አየር ጥቃት የወደመ ፋብሪካ በጋዛ

የፎቶው ባለመብት, Reuters

የምስሉ መግለጫ, በእስራኤል አየር ጥቃት የወደመ ፋብሪካ በጋዛ

በእስራኤልና በፍልስጥኤም የተነሳው ግጭት የሰላማዊ ዜጎችን ህይወት መቅጠፉን ቀጥሏል፤ ምንም እንኳን በርካታ አገራት የተኩስ አቁም ስምምነቶች ላይ እንዲደረስ ግፊት ቢያደርጉም ፍሬያማ አልሆነም። ግጭቱ ከፍ ወዳለ ጦርነት እንዳያመራም ተሰግቷል።

በባለፉት ቀናት የተሰነዘሩ የአየር ጥቃቶችና ሮኬት መወንጨፎች የበርካቶችን ህይወት ቀጥፈዋል፤ ህንፃዎችን አውድመዋል፤ በርካቶች መኖሪያ አልባ እንዲሆኑና እንዲፈናቀሉ ምክንያት ሆነዋል።

ቤታቸው በአየር ጥቃት የወደመባቸው ፍልስጥኤማውያን ቤተሰቦቻቸውን ከፍርስራሹ ለማውጣትእየሞከሩ ነበር

የፎቶው ባለመብት, Getty Images

የምስሉ መግለጫ, ቤታቸው በአየር ጥቃት የወደመባቸው ፍልስጥኤማውያን ቤተሰቦቻቸውን ከፍርስራሹ ለማውጣት እየሞከሩ ነበር

እስራኤል የምታደርገው የአየር ጥቃት ኢላማ ያደረገው የፍልስጥኤም ታጣቂዎችን ነው ብትልም በጥቃቱ የኤሌክትሪክ መስመሮች ተቋርጠዋል፤ ዋና ዋና ጎዳናዎች ፍርስርሳቸው ወጥቷል።

ከላይ በሚታየው ምስል ባለፈው ሳምንት እሁድ በእስራኤል አየር ጥቃት ቤቱ የፈረሰበት ፍልስጥኤማዊ እጥፍ ብሎ በሃዘን ተሰብሮ ይታያል።

አንዳንድ የቤተሰቦቹ አባላት በህንፃው ፍርስራሽ ተቀብረዋል።

በእስራኤል ጥቃት ቤተሰቦቿ የተገደሉባት ፍልስጥኤማዊት ሴት

የፎቶው ባለመብት, Getty Images

የምስሉ መግለጫ, በእስራኤል ጥቃት ቤተሰቦቿ የተገደሉባት ፍልስጥኤማዊት ሴት

ከሳምንት በፊት ግጭት የተነሰባት ጋዛ በርካታ ሰዎች የሞቱባት እለት በባለፈው ሳምንት መጨረሻ እሁድ ነው።

እስራኤል ከሌሊት በኋላ ባደረገችው የአየር ጥቃት እንቅስቃሴ የበዛበት ጎዳንን ኢላማ ያደረገች ሲሆን፤ በርካታ ህንፃዎች እንዳልነበሩ ወደሙ። የበርካቶችም ህይወት ተቀጠፈ።

"በጋዛ የፈረሱትን መልሶ ለመገንባት ቢያንስ አስር አመታት ያስፈልገናል" በማለት የህፃናት ዶክተር የሆኑት መሃመብ አቡ ራያ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

በግዛቲቱም ለበርካቶች የኃዘን ስነ ስርዓት ተደርጓል።

በሃማስ ሮኬት ጥቃት ምክንያት ራሳቸውን ከቦንብ ፍንዳታ ለመከላከል ወደ መጠለያ ካመሩ መካከል ይህች ህፃን አንዷ ነበረች

የፎቶው ባለመብት, Reuters

የምስሉ መግለጫ, በሃማስ ሮኬት ጥቃት ምክንያት ራሳቸውን ከቦንብ ፍንዳታ ለመከላከል ወደ መጠለያ ካመሩ መካከል ይህች ህፃን አንዷ ነበረች

ጋዛን የሚያስተዳድረው ሃማስና ሌሎች የፍልስጥኤም ታጣቂዎች ሮኬቶችን ወደ ደቡባበዊ እስራኤል በማስወንጨፍ ላይ ናቸው።

በዚህም የተነሳ ህንፃዎችና ቤቶች የፈራረሱ ሲሆን በሚሊዮን የሚቆጠሩ እስራኤላውያን ራሳቸውን ከፍንዳታ ለመከላከል ወደ ቦንብ መጠለያዎች አምርተዋል።

ከጋዛ ሰርጥ የተወነጨፈው ሮኬት ቤቷን የመታው እስራኤላዊት የደረሰውን ጉዳት ስትገመግም

የፎቶው ባለመብት, Getty Images

የምስሉ መግለጫ, ከጋዛ ሰርጥ የተወነጨፈው ሮኬት ቤቷን የመታው እስራኤላዊት የደረሰውን ጉዳት ስትገመግም

የእስራኤል መከላከያ እንዳስታወቀው ወደ ግዛታቸው ከተወነጨፉ ሮኬቶች መካከል 90 በመቶ የሚሆነውን ማክሸፋቸውን ነው።

ከዚህም በተጨማሪ ሮኬቶች ከጎረቤት አገር ሊባኖስ ወደ ሰሜን እስራኤል ተወንጭፈዋል።

በዌስት ባንክ የተገደለው ፍልስጥኤማዊው ያሲን ሃማድ ቤተሰቦች አስከሬን ሲወሰድ በኃዘን ተሞልተው እየሸኙ

የፎቶው ባለመብት, EPA

የምስሉ መግለጫ, በዌስት ባንክ የተገደለው ፍልስጥኤማዊው ያሲን ሃማድ ቤተሰቦች አስከሬን ሲወሰድ በኃዘን ተሞልተው እየሸኙ

ግጭቱ በእስራኤል ቁጥጥር ስር ወዳለችው ዌስት ባንክ ግዛት የተዛመተ ሲሆን ባለፈው ሳምንት መጨረሻ በእስራኤል ወታደሮችና በፍልስጥኤማውያን መካከል ግጭት ተፈጥሯል።

ፍልስጥኤማውያን አረቦች በዌስት ባንክ በእስራኤል ወታደራዊ አገዛዝና በተወሰነላቸው የራስ አገዛዝ ስር ይኖራሉ።

በጋዛ አየር ጥቃት ከህንፃ ፍርስራሽ የተረፉት ሪያድ ኤሽኩንታናና የስድስት አመት ሴት ልጁ በሆስፒታል ውስጥ

የፎቶው ባለመብት, Reuters

የምስሉ መግለጫ, በጋዛ አየር ጥቃት ከህንፃ ፍርስራሽ የተረፉት ሪያድ ኤሽኩንታናና የስድስት አመት ሴት ልጁ በሆስፒታል ውስጥ

ህፃኗ ለሰዓታት ያህል በቤታቸው ፍርስራሽ ውስጥ ተቀብራ የነበረ ሲሆን ከአባቷም ጋር በሆስፒታል እየታከመች ትገኛለች።

"ልጄ ይቅር በይኝ። ወደ አንቺ እንድመጣ እየነገርሸኝ ነበር፤ መምጣት አልቻልኩም" በማለት ከልጁ ጋር ሲገናኝ ፍልስጥኤማዊው ሪያድ ተናግሯል።

በአስራኤል አየር ጥቃት አባቱና የአጎቱ ልጅ የተገደለበት ፍልስጥኤማዊ ታዳጊ በአል ሺፋ ሆስፒታል እያለቀሰ

የፎቶው ባለመብት, Getty Images

የምስሉ መግለጫ, በአስራኤል አየር ጥቃት አባቱና የአጎቱ ልጅ የተገደለበት ፍልስጥኤማዊ ታዳጊ በአል ሺፋ ሆስፒታል እያለቀሰ
በእስራኤል አየር ጥቃት የ12 አመት ልጁ የተገደለችበት ራሃፍ አል ዳየር የልጁን የተሸፈነ አስከሬን ይዞ እያለቀሰ

የፎቶው ባለመብት, Getty Images

የምስሉ መግለጫ, በእስራኤል አየር ጥቃት የ12 አመት ልጁ የተገደለችበት ራሃፍ አል ዳየር የልጁን የተሸፈነ አስከሬን ይዞ እያለቀሰ

ግጭቱ ሁለተኛ ሳምንቱን የያዘ ሲሆን የአየር ጥቃቶችና ሮኬት መወንጨፎች ቀጥለዋል።

አሜሪካን ጨምሮ የአለም ኃያል አገራት የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲኖር ቢጠይቁም ምንም የተቀየረ ነገር የለም።

በጋዛ ድንበር ግጭት የተገደለ እስራኤላዊ ወታደር ቤተሰቦች እያለቀሱ

የፎቶው ባለመብት, Reuters

የምስሉ መግለጫ, በጋዛ ድንበር ግጭት የተገደለ እስራኤላዊ ወታደር ቤተሰቦች እያለቀሱ