የዝውውር ዜናዎች፡ ስተርሊንግ ወደ ዩናይትድ? ሳንቾ ወደ ቼልሲ?

ራሂም ስተርሊንግ እና ጄደን ሳንቾ

የፎቶው ባለመብት, Getty Images

የምስሉ መግለጫ, ራሂም ስተርሊንግ እና ጄደን ሳንቾ

ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀናት ብቻ በቀሩት የዝውውር መስኮት በርካታ ተጫዋቾች ወደ አዳዲስ ክለቦች ሊያመሩ ይችላሉ።

ከእነዚህ መካከል በክለባቸው ትኩረት ያጡት እንግሊዛውያኑ ራሂም ስተርሊንግ እና ጄደን ሳንቾ ይገኙበታል።

ዴይሊ ስታር እና ዴይሊ ሚረር የተሰኙት ጋዜጦች ቼልሲ እና ዩናይትድ ተጫዋቾቹን ሊቀያየሩ ይችላሉ ሲሉ ሰፋ ያለ ዘገባ ይዘው ወጥተዋል።

እንደ ዘገባዎቹ ከሆነ በቼልሲ ቤት ቦታውን በአዲሱ ፈራሚ ፔድሮ ኔቶ የተነጠቀው ስተርሊንግ ወደ ዩናይትድ ሊያቀና ይችላል።

ከቴን ሃግ ጋር ተግባብቶ መስራት ያልቻለው ሳንቾ ደግሞ በስተርሊንግ ፈንታ ወደ ቼልሲ ሊያመራ ይችላል።

ቼልሲ የብሬንትፎርድ እና የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋችን ለማስፈረም ጥረት እያደረገ ነው። ከዚህ ቀደም ቶኒ ወደ ሳውዲው አል አሃሊ ሊያመራ እንደሚችል በስፋት ሲዘገብ ነበር።

በቀጣይ ዓመት በኤቨርተን ያለው ውሉ የሚያበቃው ዶሚኒክ ካልቨርት-ሉዊን ወደ ኒውካስል ወይም ማንችስተር ዩናይትድ ሊጓዝ እንደሚችል ፉትቦል ኢንሳይደር ዘግቧል።

ሊቨርፑል ደግሞ ጣሊያናዊውን የጁቬንቱስ አጥቂ ፌዴሪኮ ቺኤዛ ከአርብ በፊት ለማስፈረም ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ ዘ አትሌቲክ ዘግቧል።

ቼልሲ ናይጄሪያዊውን የፊት መስመር ተጫዋች ቪክተር ኦሲሚሄን ለማስፈረም ከሳዑዲው አል አህሊ ጋር እየተፎካከረ መሆኑን የስፖርት ጋዜጠኛው ፍብሪዚዮ ሮማኖ ጽፏል።

አል አህሊ ለናይጄሪያዊው ተጫዋች 65 ሚሊዮን ዮሮ ለመክፈል ከናፖሊ ጋር ተስማምቷል። አል አህሊ ተጫዋቹን ለማሳመን ጥረት እያደረገ ይገኛል።

ሳውዝሃፕተን የአርሰናሉን ሁለተኛ ግብ ጠባቂ አረን ራምስዴል ለማስፈረም በዝርዝሩ ውስጥ መያዙ ተገልጿል።

የተረጋገጡ የዝውውር ዜናዎች

የአርሰናል የፊት መስመር ተጫዋች ኤዲ ኒኪታህ ወደ ክርስታል ፓላስ ለማቅናት ከጫፍ ደርሷል።

ፋብሪዚዮ ሮማኖ የ25 ዓመቱ አጥቂ በ25 ሚሊዮን ፓዎንድ ወደ ፓላስ እንደሚዘዋወር ዘግቧል።

የማንቸስተር ሲቲው ጆአ ካንሴሎ ወደ ሳውዲ ፕሮ ሊግ ተዘዋውሯል። በውስት ባርሴሎና የነበረው ካንሴሎ በ21 ሚሊዮን ፓዎንድ የሳውዲውን አል-ሂላል ተቀላቅሏል።

ካንሴሎ እአአ 2019 ላይ ከጁቬንቱስ ሲቲን ከተቀላቀለ በኋላ የጋርዲዮላ ቁልፍ ተጫዋች ሆኖ ቆይቶ ነበር።

ይሁን እንጂ ተጫዋቹ ከጋርዲዮላ ጋር መግባባት ሳይችል ቀርቶ ወደ ሚዩኒክ እና ባርሴሎና በውሰት ተሰጥቶ ቆይቷል።

አርሰናል የሚኬል ሜሪኖን ዝውውር በመጨረሻም አጠናቋል። የ28 ዓመቱ ስፔናዊ አማካይ ዝውውር ለበርካታ ሳምንታት ሲዘገብ ቆይቶ የዝውውሩን መጠናቀቅ የሰሜን ለንደኑ ክለብ ትናንት ይፋ አድርጓል።

የ X ይዘትን ይለፉት
ይዘቱን X ይፈቅዳሉ?

ይህ ጽሑፍ በX. የቀረበ ይዘት ይዟል። ገጹ ቴክኖሎጂዎች ወይም ኩኪዎች ሊኖረው ስለሚችል ገጹ ከመከፈቱ በፊት የእርስዎን ፍቃድ እንጠይቃለን። ፍቃድዎን ከመስጠትዎ በፊት የX ኩኪ ፖሊሲ እና የ ማንበብ ይፈልጉ ይሆናል። ይዘቱን ለማንበብ ‘እቀበላለሁ ቀጥል’ የሚለውን ይምረጡ።

ማሳሰቢያ: በሌሎች ገጾች ላይ ላሉ ይዘቶች ቢቢሲ ኃላፊነት አይወስድም።

የ X ይዘት መጨረሻ

ሊቨርፑል ደግሞ የጆርጂያ ብሔራዊ ቡድን ግብ ጠባቂን ጂኦርጂ ማማረዳሸቪሊ ከቫሌንሺያ አስፈርሟል።

ተጫዋቹ ሊቨርፑልን በ29 ሚሊዮን ፓዎንድ መቀላቀሉ ቢዘገብም የእንግሊዙን ክለብ የሚቀላቀለው በ2025/26 የውድድር ዘመን ነው ተብሏል።

ዩናይትድ ለአማካይ ስፍራው ቀዳሚ ተመራጩ ያደረገውን ማኑኤል ኡጋርቴን ለማስፈረም ከስምምነት ደርሷል።

ማንቸስተር ዩናይትድ ለኡጋርቴ 42 ሚሊዮን እንደሚከፍል ተዘግቧል።

ከፒኤስጂ ወደ ዩናይትድ የሚዘዋወረው ኡራጋዩ ኡጋርቴ በዚህ የዝውውር መስኮት አምስተኛ የቴን ሃግ ፈራሚ ይሆናል።