የ2020 ቶኪዮ ኦሊምፒክ፡ በቶኪዮ ኦሊምፒክ የሚጠበቁ ኢትዮጵያውያንና አፍሪካውያን ተወዳዳሪዎች እነማን ናቸው?

አፍሪካውያን ሯጮች በተለይም ኢትዮጵያውያንና ኬንያውያን አትሌቶች በመካከለኛ እና በረጅም ርቀት የሩጫ መስኮች በኦሊምፒክ ውድድሮች ላይ የበላይ ናቸው።

ባለፈው ዓመት ሊካሄድ ታቅዶ በኮሮናቫይረስ ወረርሽን ምክንያት ወደዚህ ዓመት የተሸጋገረው የቶኪዮ ኦሊምፒክ ከዚህ በፊት በውድድሩ ውስጥ ያልነበሩ ስፖርቶችን በማካተት በዚህ ሳምንት መካሄድ ይጀምራል።

በዚህም መሰረት አምስት የስፖርት አይነቶች በውድድሩ ውስጥ እንደተካተቱ ታውቋል፤ እነሱም የውሃ ላይ ሸርተቴ (ሰርፊንግ)፣ ተራራ መውጣት (ክላይምቢንግ)፣ ቤዝቦል፣ ስኬት ቦርዲንግ እና ካራቴ ሲሆኑ የተወሰኑ አፍሪካውያን በእነዚህ ዘርፎቹ ይወዳደራሉ።

አርብ ሐምሌ 16/2013 ዓ.ም የቶኪዮው ኦሊምፒክ ሲጀምር በተለያዩ ስፖርት ውድድሮች የሚሳተፉ በርካታ አፍሪካውያን ሲኖሩ ኢትዮጵያም በኦሊምፒክ ስሟ በሚጠራባቸው ዘርፎች የሚሳተፉ ስፖርተኞችን ልካለች።

ከኢትዮጵያውያን በተጨማሪ በርካታ አገራት በተለያዩ ዘርፎች በውድድሩ ይሳተፋሉ ከእነዚህ መካከል በቶኪዮው ኦሊምፒክ ላይ ትኩረት ከተደረገባቸው መካከል ከስኬታማዎቹ እና ከአዲሶቹ መካከል የተወሰኑትን ወድድር ዘርፎቹ እንዲህ አቅርበናል።

ሥነ ዘዴ

እነዚህ የአፍሪካ ስፖርተኞች የተለያዩ የአህጉሪቱን ክልሎች ይወክላሉ ተብለው ነው የቀረቡት። የተመረጡትም በኦሊምፒክ ተሳትፏቸው፣ ባገኙት ሜዳሊያ ብዛት እና ከሚወዳደሩበት የተለየ የስፖርት አይነት አንጻር ነው።

ተሳታፊዎች

የአርትኦት ዝግጅት፡ ንኬቺ ኦግቦና፣ ፕሪንሰስ አቡሜሬ እና ሙቶኒ ሙቺሪ። ዲዛይን፡ ኦላኒዬ አዴቢምፔ እና ሚሊሰንት ዋቺራ። የድረ ገጽ ዝግጅት፡ ፒዩሪቲ ቢሪር። ተጨማሪ፡ ሳሊ ሞራሌስ እና ሴሌስቲን ካሮኔይ

ምስሎች፡

ጌቲ ኢሜጅስ፣ የዓለም ቅርጫት ኳስ ፌዴሬሽን፣ ኤኤፍፒ፣ ናይጄሪያን ኒውስ፣ የናይጄሪያ የውሃ ስፖርቶች ፌዴሬሽን፣ መክሰብ ደበሳይ፣ የሞዛምቢክ የውሃ ቀዘፋ ቡድን፣ ጊያና ፋሩክ፣ ኢፒኤ፣ ፕሬስፎከስ/ኒውስ ፒክስ እና ፒኤ፣ ኤርዊዘርየት ትዊተር፣ ብሩስ ቫይን እና ኦሊምፒክ፣ ክላይምብ ዛምቢያ፣ ዲደብሊው እና የሞዛምቢክ ቡድን።