ይህ ዝቅተኛ ዳታን በመጠቀም ጽሑፍ ብቻ የሚቀርብበት የቢቢሲ አማርኛ ድረ ገጽ ነው
በኢትዮጵያ የ71 ሰዎችን ሕይወት የቀጠፈው የትራፊክ አደጋ
አደጋው የደረሰው በዞኑ ቦና ዙሪያ ወረዳ ዕሁድ ታኅሳስ 20/ 2017 ዓ.ም. ከሰዓት 11:00 አካባቢ 'አይሱዚ' በተባለ የጭነት ተሽከርካሪ "ወደ ሙሽራዋ ቤት" እየተጓዙ የነበሩ ሰርገኞች ላይ ነው።
ሰርገኞቹ ሚሪዴ ከተባለ ቀበሌ ቤተ ክርስቲያን ደርሰው ወራንቻ ወደተባለ አካባቢ ሲጓዙ ጋለና ወንዝ ድልድይ ላይ ተሽከርካሪው መስመር በመሳት "ተወርውሮ" ወደ ወንዙ መግባቱን የአካባቢው ባለስልጣናት ተናግረዋል።
ሰርገኞችን አሳፍሮ የነበረ ተሽከርካሪ ወደ ወንዝ በመግባቱ ነው አደጋው የተከሰተው ሲሉ ትራፊክ ፖሊስ ሳጅን እጅጉ ይልማ ይናገራሉ።