የጥምቀት አከባበር በምሥል

በመላው ኢትዮጵያ የክርስትና እምነት ተከታዮች የኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀት በዓልን እያከበሩ ነው።

የጥምቀት በዓል ከዋዜማው ጥር 10 ጀምሮ ጥር 11 የሚከበር ሲሆን ጥር 12 ደግሞ የቃና ዘገሊላ በዓል እንዲሁ በድምቀት ይከበራል።

ከጥምቀት በዓል ዕለት ቀደም ብሎ ባለው ቀን በሚከበረው የከተራ በዓል፤ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አብያተ ክርስቲያናት ታቦታት ወጥተው የጥምቀት በዓል ወደሚከበርባቸው ቦታ በሕዝብ ታጅበው ይጓዛሉ።

አዲስ አበባ የሚገኘው ጃን ሜዳ እና ጎንደር ጥምቀት በተለየ ሁኔታ የሚከበርባቸው ሥፍራዎች መካከል ሲሆኑ፤ ከምዕመናን በተጨማሪ የተለያዩ አገራት ቱሪስቶች በዓሉን ለመታደም ይመጣሉ።

ከተለያዩ የአገሪቱ ከተሞች የዛሬውን የበዓሉ አከባበር የሚያሳዩ ምሥሎችን እንዲህ አጠናቅረናል።