ዜና አንባቢዋ በቀጥታ የቴሊዚዥን ስርጭት ላይ የፊት ጥርሷ ወለቀ

የፎቶው ባለመብት, Instagram
በቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት ላይ ከቴክኒክ ብልሽት ጀምሮ ብዙ ያልታሰቡ እክሎች ሊፈጠሩ ይችላሉ።
ዩክሬናዊቷ የቴሌቪዥን ዜና አምባቢ ማሪችካ ፓዳልኮ በዚህ ሳምንት ያጋጠማት ግን የለየ ነገር ነበር። ፓዳለኮ ዜና እያነበበች ሳለ ከፊት ጥርሶቿ መካከል አንዱ ወልቋል።
ይሁን እንጂ ዜና አንባቢዋ በፍጹም እርጋታ ሳትደናገጥ በቀኝ እጇ ጥርሷን ከአፏ አውጥታ በመያዝ ምንም እንዳልተፈጠረ ዜና ማንበቧን ቀጥላለች።
"እውነት ለመናገር የተፈጠረው ነገር ማንም ሰው ሳያስተውለው ያልፋል ብዬ ነበር" ስትል በኢንስታግራም ገጿ ላይ ጽፋለች።
ፓዳልኮ ዜና እያነበበች ሳለ ጥርሷ ሲወልቅ የሚያሳየው ምስል ግን በማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ዘንድ በስፋት ለመሰራጨት ጊዜ አልወሰደበትም ነበር።
"ተመልካቾች ምን ያህል በአጽንኦ እንደሚመለከቱን አሳንሼ ገምችያለሁ" በማለት ዜና ስታነብ የፊት ጥሯ ሲወልቅ የሚያሳየውን ቪዲዮ አያይዛ በኢንስታግራም ገጿ ላይ አስፍራለች።
ይህ ጽሑፍ በInstagram. የቀረበ ይዘት ይዟል። ገጹ ቴክኖሎጂዎች ወይም ኩኪዎች ሊኖረው ስለሚችል ገጹ ከመከፈቱ በፊት የእርስዎን ፍቃድ እንጠይቃለን። ፍቃድዎን ከመስጠትዎ በፊት የInstagram ኩኪ ፖሊሲ እና የ ማንበብ ይፈልጉ ይሆናል። ይዘቱን ለማንበብ ‘እቀበላለሁ ቀጥል’ የሚለውን ይምረጡ።
የ Instagram ይዘት መጨረሻ

ዜና አንባቢዋ ማሪችካ ፓዳልኮ ከ10 ዓመታት በፊት በድንገተኛ አደጋ ሴት ልጇ ጥርሷ ላይ ጉዳት አደርሳባት ህክምና ተደርጎላት እንደነበረም አስታውሳለች።
ምንም እንኳ የቴሌቪዥን ጣቢያው ዜና አምባቢዋ ጥርሷ ሲወልቅ የሚያሳየውን ምስል በዩቲዩብ ላይ ባይጭነውም፤ ማሪችካ ከበርካቶች ያገኘችው ድጋፍ እና ማበረታቸው እንዳስደነቃት ተናግራለች። በዚህም በእራሷ የኢንስታግራም ገጽ ላይ ምስሉን አጋርታለች።
"በየትኛውም አይነት ሁኔታ ውስጥ፤ እርጋታ ያስፈልጋል" ካለች በኋላ ለቀጣዩ ዜና "ነገ ጠዋት እንገናኛለን" ብላለች።












