ይህ ዝቅተኛ ዳታን በመጠቀም ጽሑፍ ብቻ የሚቀርብበት የቢቢሲ አማርኛ ድረ ገጽ ነው
ፕሬዚዳንት ኤማኑኤል ማክሮን ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ስምምነቶች ላይ ደርሰዋል
ዛሬ ጠዋት መጋቢት 4 ኢትዮጵያና ፈረንሳይ በሂልተን ሆቴል የተለያዩ ስምምነቶችን ተፈራርመዋል።
ሁለቱ ኃገራት ስምምነት ከደረሱባቸው ዘርፎች መካከል የፈረንሳይ ኢቬስትመንትን በኢትዮጵያ ለማበረታት፣ የኢትዮጵያን ምጣኔ ኃብት ለውጦችን ለማገዝ የሚደረጉ የገንዘብ ድጋፍና የባህልን ጥበቃ ይገኙበታል።
በኢትዮጵያ የሚገኘው የፈረንሳይ ኤምባሲ ሰራተኛ መሳይ ፈጠነ ለቢቢሲ እንደገለፀው ከሰአት እጥረት አንፃር ቃለ መጠይቅ ማድረግ አይቻልም ቢባልም ለተለያዩ ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል።
የስምምነቶቹ ፈራሚዎች ስም ዝርዝር ከዚህ በታች እንደሚከተለው ነው።
1) ደ/ር ዦ ኢቭ ለ ጋል እና ዶ/ር ሰለሞን በላይ ተሰማ የጠረፍ ትብብር ተፈራርመዋል
2) አቶ ቤርናር ኩሌ እና አቶ ተመስገን ጥላሁን ለሶምዲያ ፋብሪክ የስምምነት ሰነድ ተፈራርመዋል
3) አቶ ሮዶልፍ ሳዴ እና አቶ ሙሉጌታ አሰፋ ለጭነት ሎጂስቲክስ የሽርክና ንግድ የስምምነት ሰነድ ተፈራርመዋል
4) አቶ ሮዶልፍ ሳዴ እና አቶ ሮባ መገርሳ ለከፍተኛ ትምህርት ፈተናዎች የትብብር ፍላጎት ማሳያ ስምምነት
5) አቶ ቲዬሪ ዴዮ፣ ወ/ሮ ማሪ ላም ፍሬዶ እና አቶ ጥላሁን ታደሰ ለኮንስትራክሽን የትብብር ፍላጎት ማሳያ ስምምነት
6) አቶ ማክሲም ሳዳ እና አቶ ቴዎድሮስ አብራሃም ለቴሌቪዥን ፕሮግራም የስምምነት ሰነድ ተፈራርመዋል
7) አቶ ፓትሪክ ጌሬንቶን እና አቶ ቴዎድሮስ አብርሃም ለትራንስፖርትና የጭነት ሎጂስቲክስ የሽርክና ንግድ የስምምነት ሰነድ ተፈራርመዋል
የስምምነቱ ፊርማ ታዛቢዎችም ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ናቸው
1) የኢትዮጵያ ፋይናንስ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሺዴ
2) የአውሮፓ የውጪ ፉዳይ ሚኒስትር አቶ ዦ ኢቭ ለ ድሪያ
3) የከፍተኛ ትምህርት ምርምርና ፈጠራ ሚኒስትር ወ/ሮ ፍሬዴሪክ ቪዳል
4) የኢትዮጵያ ግዛት ሚኒስትር ዶ/ር ሹመቴ ግዛው
5) ከአስተዳደር ሚኒስቴርና ኢኮሎጂካል እና ተካታዊ ሽግግር ጋር የሚሠራው የፈረንሳይ ግዛት ሚኒስትር ወ/ሮ ብሩን ፕዋርሶ
6) ምክትል ኮሚሽነር አቶ ተመስገን ጥላሁን
የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኤማኑኤል ማክሮ ትናንት መጋቢት 3 ቀን ለሁለት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት ነበር ኢትዮጵያ የገቡት።
የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን ከጎበኙ በኋላ ጉዟቸውን ወደ አዲስ አበባ ያቀኑ ሲሆን ዛሬ ከአፍሪካ ሕብረት ሊቀመንበር ጋር እንደሚገናኙም ተነግሯል።