'ጋዛ እየነደደች ነው': በከባድ የአየር ድብደባ መካከል እስራኤል የጀመረችው የእግረኛ ሠራዊት ጥቃት

ከአንድ ሳምንት በኋላ ሁለት ዓመት የሚሞላው እስራኤል በጋዛ ላይ እያካሄደችው ያለው መጠነ ሰፊ ወታደራዊ ዘመቻ አሁን ተባብሶ ቀጥሏል።

እስራኤል ጋዛን ለመቆጣጠር ባወጣችው ዕቅድ መሠረት ከባድ የአየር ድብደባ እና የእግረኛ ሠራዊት ጥቃት በጋዛ ላይ ከፍታለች።

በዚህም ጋዛ ውስጥ ያሉ ሕንጻዎች በእስራኤል የጦር አውሮፕላኖች እየወደሙ ሲሆን፣ ይህንንም የእስራአል የመከላከያ ሚኒስትር ኢዝራኤል ካትዝ "ጋዛ እየነደደች ነው" ሲሉ ገልጸውታል።

መስከረም 26/2016 ዓ.ም. ሐማስ ባልተጠበቀ ሁኔታ በእስራኤል ላይ የፈጸመውን ጥቃት ተከትሎ 1200 ሰዎችን ከገደለ እና 251 ሰዎችን ካገተ በኋላ እስራኤል በጋዛ ላይ ከባድ ጥቃት ስትፈጽም ቆይታለች።

በሐማስ የሚመራው የጋዛ ጤና ሚኒስቴር እንዳለው ከ60 ሺህ በላይ የጋዛ ነዋሪዎች ተገድለዋል። አሁን የተከፈተው ጥቃት ደግሞ የሚሞቱትን ሰዎች ቁጥር እንደሚጨምረው ተሰግቷል።

እነዚህ ፎቶግራፎች በጋዛ ውስጥ ያለውን ሁኔታ በጥቂቱ የሚያሳዩ ናቸው።