ይህ ዝቅተኛ ዳታን በመጠቀም ጽሑፍ ብቻ የሚቀርብበት የቢቢሲ አማርኛ ድረ ገጽ ነው
ተዋናይ ታሪኩ ብርሃኑ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ
በበርካታ ፊልሞች በመተወን በኢትዮጵያ ፊልም ኢንዱስትሪ ዝናን ያተረፈው አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።
የተለያዩ የኃገር ውስጥ ሚዲያዎች እንደዘገቡት ተዋናዩ በህመም ላይ እንደነበረና ለሳምንታትም በህክምና ሲረዳ እንደቆየም ነው።
በቅጽል ስሙ ባባ በሚል የሚታወቀው አርቲስቱ ህመሙ ምን እንደነበር አልተገለጸም።
ከአርባ ያህል ፊልሞች የተወነው ታሪኩ ወንድሜ ያዕቆብ፣ ላውንድሪ ቦይ፣ ማርትሬዛ፣ ይመችሽ-የአራዳ ልጅ 2፣ ሞኙ የአራዳ ልጅ 4 በፊልም ታዳሚያን ዘንድ ተወዳጅነትን ካተረፈባቸው መካከል የተወሰኑት ናቸው።
በተጫማሪም አንድ ሁለት፣ ብር ርርር፣ ወደው አይሰርቁ፣ ወፌ ቆመች፣ እንደ ቀልድ፣ ወጥቶ አደር፣ አባት ሀገር የሚሉት ፊልሞችም አርቲስቱ ከተወነባቸው ውስጥ የሚጠቀሱ ናቸው።
አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ የአንድ ልጅ አባት እንደነበርም ተዘግቧል።
በርካቶች የአርቲስቱ አድናቂዎች ኃዘናቸውን በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች እየገለጹ ሲሆን “ገና መስራት በሚችልበት በለጋ እድሜው በመቀጠፉም አዝነናል” ብለዋል።