ይህ ዝቅተኛ ዳታን በመጠቀም ጽሑፍ ብቻ የሚቀርብበት የቢቢሲ አማርኛ ድረ ገጽ ነው
ጭምቅ ሀሳብ
- የሕዳሴ ግድብ ዛሬ ማክሰኞ፣ ጳጉሜ 4/ 2017 ዓ.ም የጎረቤት አገራት መሪዎች በተገኙበት ተመረቀ።
- በምረቃ ሥነ ስርዓቱ ላይ የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ፣ የደቡብ ሱዳኑ ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት፣ የጂቡቲው ፕሬዚዳንት እስማኤል ኦማር ጊሌህ እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በሚቀጥሉት ጥቂት ዓመታት በ30 ቢሊዮን ዶላር ሜጋ ፕሮጀክቶች እንደሚጀመሩ አስታወቁ።
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሕዳሴው ግድብ ምረቃ ላይ ባደረጉት ንግግር ግድቡ ለጥቁር ሕዝቦች ታሪክ ሆኖ የሚቆይ ነው አሉ።
- የኬንያ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የምህንድስና ምኞት ብቻ ሳይሆን አፍሪካ እጣ ፈንታዋን እንደምትወስን ደማቅ ማረጋገጫ ነው ብለዋል።
- የባርቤዶስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሚያ ሞትሊ በበኩላቸው ግድቡ የዓድዋ ድል ተምሳሌት በምህንድስና ጥበብ ዳግም ተገልጦ ነው ሲሉ አሞካሽተዋል።
- የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ እስካሁን ድረስ 233 ቢሊየን ብር ወጥቶበታል።