ይህ ዝቅተኛ ዳታን በመጠቀም ጽሑፍ ብቻ የሚቀርብበት የቢቢሲ አማርኛ ድረ ገጽ ነው
ለጉብኝት ክፍት የተደረገው የቀድሞው ማዕከላዊ እሥር ቤት በፎቶ
የቀድሞው ማዕከላዊ እሥር ቤት ዛሬ ለጉብኝት ክፍት ተደርጓል። ከዛሬ ጀምሮ እስከ ጳጉሜን 4 ቀን 2011 ዓ. ም. እሥር ቤቱ ለሕዝብ እይታ ክፍት እንደሚሆን የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ አስታውቋል።
ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት ይፈጸምበት ነበር የሚባለው ማዕከላዊ እሥር ቤት፤ ጳጉሜን 5 ቀን 2011 ዓ. ም. የሚከበረውን የፍትህ ቀን ምክንያት በማድረግ ለሕዝብ እይታ ክፍት መደረጉንም የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ አስታውቋል።
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ እሥር ቤቱን ጎብኝተዋል።
በቦታው የሚገኘው ባልደረባችን ካነሳቸው ፎቶግራፎች ጥቂቱን እናካፍላችሁ፦