ኮሮናቫይረስ፡ የእንቅስቃሴ ገደብ በተጣለባቸው አገራት ያሉ ሙስሊሞች ረመዳንን እንዴት እያሳለፉ ነው?

የፎቶው ባለመብት, AFP
የኮሮናቫይረስ ስርጭትን ለመግታት አገራት ያሳለፉትን እርምጃዎች ተከትሎ መስጊዶች በመዘጋታቸውና መሰባሰብ በመከልከሉ ምክንያት በዓለም ላይ ያሉ በሚሊየን የሚቆጠሩ ሙስሊሞች ዘንድሮ ረመዳንን በተለየ መንገድ እያሳለፉ ነው።
በሙስሊሙ ማህበረሰብ ዘንድ ትልቅ ቦታ በሚሰጠው የረመዳን ወር፤ 1.8 ቢሊየን የዓለማችን ህዝቦች ጎህ ሲቀድ ጀምሮ ፀሐይ እስክትጠልቅ ከምግብ፣ ከመጠጥ፣ ከሲጋራ እንዲሁም ከግብረ ስጋ ግንኙነት የሚታቀቡበት ነው።
በዚህ ወቅት ቤተሰብና ወዳጆች ሰብሰብ ብለው ማፍጠር፣ በሕብረት ማምለክና መስገድ የተለመደ ነው።
ይሁን እንጅ በዚህ ዓመት ይህንን የተቀደሰ የፆም ወር ብቻቸውን በቤታቸው እንዲያሳልፉ ተገደዋል።
በእየሩሳሌም የሚገኘው አል አቅሳ መስጊድ ግቢ ከባለፈው ወር አጋማሽ ጀምሮ ተዘግቷል፤ ለረመዳንም አይከፈትም። የእስልምና ቅዱስ ከተማ ተብላ የምትጠራዋ የሳዑዲ አረቢያዋ መካም በቫይረሱ ተጠቅታለች። ለመሆኑ ረመዳን በተለያዩ አገራት እንዴት እያለፈ ነው?

የፎቶው ባለመብት, AFP

የፎቶው ባለመብት, Reuters

የፎቶው ባለመብት, AFP

የፎቶው ባለመብት, Reuters

የፎቶው ባለመብት, Reuters










