የተከሰከሰው አውሮፕላን የመረጃ ሳጥን ወደ ፈረንሳይ ተወሰደ

የአውሮፕላኑ ክፍሎች

የፎቶው ባለመብት, Jemal Countess

እሁድ መጋቢት 1 ቀን 2011 ዓ.ም ከአዲስ አበባው ቦሌ አለም ዓቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተነስቶ ወደ ናይሮቢ ሲበር ቢሾፍቱ አቅራቢያ የተከሰከሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ቦይንግ 737-8 ማክስ የበረራ ቁጥር ET 302 አውሮፕላን መረጃ ሳጥን በፈረንሳይ አገር እንዲመረመር ዛሬ ወደ ፓሪስ መወሰዱን ኢትዮጵያ አየር መንገድ በትዊተር ገፁ አስፍሯል።

የ X ይዘትን ይለፉት
ይዘቱን X ይፈቅዳሉ?

ይህ ጽሑፍ በX. የቀረበ ይዘት ይዟል። ገጹ ቴክኖሎጂዎች ወይም ኩኪዎች ሊኖረው ስለሚችል ገጹ ከመከፈቱ በፊት የእርስዎን ፍቃድ እንጠይቃለን። ፍቃድዎን ከመስጠትዎ በፊት የX ኩኪ ፖሊሲ እና የ ማንበብ ይፈልጉ ይሆናል። ይዘቱን ለማንበብ ‘እቀበላለሁ ቀጥል’ የሚለውን ይምረጡ።

ማሳሰቢያ፡ የሦስተኛ ወገን ይዘቶች ማስታወቂያ ሊኖራቸው ይችላል

የ X ይዘት መጨረሻ

ጀርመን የመረጃ ሳጥኑን እንድትመረምር ተጠይቃ ሶፍትዌሩ እንደሌላት በመግለፅ ጥያቄውን ሳትቀበል መቅረቷ ተገልፆ ነበር ትናንት።

የመረጃ ሳጥኑ ወደ ፓሪስ የሄደው በአለም አቀፉ አቪዬሽን አደጋ ምርመራ ቢሮ በሚመራው የኢትዮጵያ ልዑክ ነው።

በአደጋው 157 ሰዎች ሞተዋል።

አደጋው አካባቢ የተገኙ ነገሮች

የፎቶው ባለመብት, Jemal Countess