የተከሰከሰው አውሮፕላን የመረጃ ሳጥን ወደ ፈረንሳይ ተወሰደ

የፎቶው ባለመብት, Jemal Countess
እሁድ መጋቢት 1 ቀን 2011 ዓ.ም ከአዲስ አበባው ቦሌ አለም ዓቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተነስቶ ወደ ናይሮቢ ሲበር ቢሾፍቱ አቅራቢያ የተከሰከሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ቦይንግ 737-8 ማክስ የበረራ ቁጥር ET 302 አውሮፕላን መረጃ ሳጥን በፈረንሳይ አገር እንዲመረመር ዛሬ ወደ ፓሪስ መወሰዱን ኢትዮጵያ አየር መንገድ በትዊተር ገፁ አስፍሯል።
የ X ይዘትን ይለፉት
ይዘቱን X ይፈቅዳሉ?
ማሳሰቢያ፡ የሦስተኛ ወገን ይዘቶች ማስታወቂያ ሊኖራቸው ይችላልይህ ጽሑፍ በX. የቀረበ ይዘት ይዟል። ገጹ ቴክኖሎጂዎች ወይም ኩኪዎች ሊኖረው ስለሚችል ገጹ ከመከፈቱ በፊት የእርስዎን ፍቃድ እንጠይቃለን። ፍቃድዎን ከመስጠትዎ በፊት የX ኩኪ ፖሊሲ እና የ ማንበብ ይፈልጉ ይሆናል። ይዘቱን ለማንበብ ‘እቀበላለሁ ቀጥል’ የሚለውን ይምረጡ።
የ X ይዘት መጨረሻ
ጀርመን የመረጃ ሳጥኑን እንድትመረምር ተጠይቃ ሶፍትዌሩ እንደሌላት በመግለፅ ጥያቄውን ሳትቀበል መቅረቷ ተገልፆ ነበር ትናንት።
የመረጃ ሳጥኑ ወደ ፓሪስ የሄደው በአለም አቀፉ አቪዬሽን አደጋ ምርመራ ቢሮ በሚመራው የኢትዮጵያ ልዑክ ነው።
በአደጋው 157 ሰዎች ሞተዋል።

የፎቶው ባለመብት, Jemal Countess









