የኬፕታውን ባለስልጣናት ሃገር በቀል ያልሁኖ ዛፎችን ሊያስወግዱ ነው የሚሉና ሌሎች አጫጭር ዜናዎች

የፎቶው ባለመብት, DEA / L. ROMANO
አፍሪካ
• ዚምባብዌ ውስጥ አንድ የህዝብ ማመላለሻ መኪና በእሳት ተቀጣጥሎ የ42 ሰዎች ህይወት አለፈ።
እሳቱ የተነሳው አንድ ተሳፋሪ የያዘው የሲሊንደር ጋዝ ፈንድቶ እንደሆነ ተገልጿል።
• ሞሮኮ በሰአት 320 ኪሎሜትር የሚጓዘውን በአፍሪካ ፈጣኑን ባቡር ዛሬ አስመረቀች።
ሙሉ ወጪው 2.4 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን፤ ለማጠናቀቅ ሰባት ዓመት ፈጅቷል።
• አልፕስ ተራሮችን አቋርጠው ወደ ፈረንሳይ ሊገቡ የነበሩ 10 አፍሪካውያን ወጣቶች በበረዶ ምክንያት በፖሊስ ተያዙ።
ወጣቶቹ በረዶው ከአቅማቸው በላይ ስለሆነባቸው መንቀሳቀስ አልቻሉም።
• በደቡብ አፍሪካ የኬፕታውን ከተማ ባለስልጣናት እንደ ባህር ዛፍ ያሉ ሃገር በቀል ያልሆኑ ዛፎችን ልናስወግድ ነው ብለዋል።
ምክንያታቸው ደግሞ ተክሎቹ ከፍተኛ የውሃ እጥረት እንዲከሰት አድርገዋል የሚል ነው።
• አሜሪካ አፍሪካ የምታሰማራቸውን ወታደሮቿን በሚቀጥሉት ዓመታት 10 በመቶ ልትቀንስ ነው።
7200 የአሜሪካ ወታደሮች በአፍሪካ የሚገኙ ሲሆን፤ ከዚህ በኋላ የመረጃ ድጋፍና ምክር ላይ ትኩረት ይደረጋል ተብሏል።
ጣልያን
• ጣልያን ውስጥ በቁንጅና ውድርድ የመጨረሻ ዙር የደረሰች ሞዴል ላይ አሲድ የደፋው ግለሰብ የ15 ዓመት እስራት ተፈረደበት።
ጌሲካ ኖታሮ የተባለችው ሴት አሁን ከጉዳቷ አገግማ የቴሌቪዥን ፕሮግራም አዘጋጅ ሆናለች።
አሜሪካ
• አሜሪካ ውስጥ ለአንድ የጎዳና ተዳዳሪ 400 ሺ ዶላር እርዳት ያሰባሰቡት ባልና ሚስት ፍርድ ቤት ቀረቡ።
ሰዎቹ ከጎዳና ተዳዳሪው ጋር በመተባበር ገንዘብ ለማግኘት የውሸት ታሪክ ፈጥረዋል በሚል ክስ ነው ፍርድ ቤት የቀረቡት።
ህንድ
• ህንድ ውስጥ እናታቸው በቅርቡ በሰዎች የተገደለችባቸው ሁለት ነብሮች ጥቃት ከማድረሳቸው በፊት እየተፈለጉ ነው።
እናትየው 13 ሰዎችን የገደለች ሲሆን ለሁለት ዓመታት ስትፈለግ ነር።
ካምቦዲያ
• የቀድሞው የካምቦዲያ ፕሬዝዳንትና ምክትላቸው በዘር ማጥፋት ወንጀል ክስ ተመሰረተባቸው።
የ87 እና የ92 ዓመት የቀድሞ ባለስልጣናቱ ሙስሊሞችንና ቬትናማውያንን በመጨፍጨፍ ነው የከተሰሱት።












