ማንነታቸው ያልታወቀ 40 ታጣቂዎች በመቀሌ አውሮፕላን ማረፊያ

መቀሌ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፊያ

የፎቶው ባለመብት, Geez media

ማንነታቸው ያልታወቀ 40 የታጠቁ ወታደሮችን ይዞ ትግራይ ክልል የገባ አንቶኖቭ አውሮፕላን በመቀሌ አሉላ አባ ነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ተያዙ።

ምንጮች ለቢቢሲ እንደገለፁት በአውሮፕላኑ ውስጥ የነበሩት የታጠቁ ወታደሮች ተልዕኮና ማንነታቸው ባይታወቅም ኢትዮጵያዊያን እንደሆኑ አመልክተዋል።

ከሁለት ቀናት በፊት ከሱዳን በኩል ወደ ኢትዮጵያ እንደገባ የተጠረጠረው አንቶኖቭ አውሮፕላንና አሳፍሯቸው የነበሩት 40 የታጠቁ ወታደሮች በመቀሌው የአሉላ አባ ነጋ አውሮፕላን ማረፊያ መያዛቸውን ስማቸው እንዳይጠቀስ የክልሉ ባለስልጣን በአካባቢው ለሚገኘው የቢቢሲ ዘጋቢ ገልፀዋል።

ምንጮቹ ጨምረው ወታደሮቹ አንቶኖቭ ተብሎ በሚታወቀው ግዙፍ አውሮፕላን በአሉላ አባ ነጋ አየር ማረፊያ በድንገት ያረፉት በስህተት መሆኑን ገልፀው፤ የክልሉ ፖሊስ ጉዳዩን እየመረመረው እንደሚገኝ ተናግረዋል።