ናይሮቢ፡ የሟቾች ቁጥር 21 ደርሷል

የሟቾች ቁጥር 21 ደርሷል፤ 19 የደረሱበት አልታወቀም

የፎቶው ባለመብት, Getty Images

በናይሮቢው ዱሲት2ናይሮቢ ሆቴል በደረሰው የሽብር ጥቃት የሟቾች ቁጥር 21 መድረሱን መንግሥት ይፋ አድርጓል።

በጥቃቱ ጉዳት የደረሰባቸው 28 ሰዎች ደግሞ የህክምና አገልግሎት ለማግኘት በሆስፒታል ይገኛሉ። የኬንያ ቀይ መስቀል ማኅበር እስካሁን ድረስ 19 ሰዎች የደረሱበት አልታወቀም ብሏል።

የኬንያ ፖሊስ አሸባሪዎቹን ገድሎ ህንጻውን ለመቆጣጠር የ19 ሰዓታት ኦፕሬሽን ማካሄድን ነበረበት። ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ፤ ''አሸባሪዎቹ በሙሉ ተገድለዋል፤ ኦፕሬሽኑም ተጠናቋል'' ሲሉ አሳውቀል።

አል ሸባብ ለጥቃቱ ኃላፊነቱን እወስዳለሁ ማለቱ ይታወሳል።

ሮይተርስ እንደዘገበው፤ አል ሸባብ "ይህን ጥቃት የሰነዘርኩት ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እየሩሳሌምን የእስራኤል ዋና ከተማ አድርገው በመቁጠራቸው ምላሽ እንዲሆን ነው" ብሏል።

እየሩሳሌም ለእስልምና፣ ለክርስትና እና ለአይሁድ እምነት ቅድስት ስፍራ ተደርጋ ትወሰዳለች። እስራኤል አጠቃላይ የእየሩሳሌም ክፍልን መዲናዋ አድርጋ ትቆጥራለች። ፍልስጤሞች በበኩላቸው ምስራቃዊ እየሩሳሌም ወደፊት እውቅና ለምታገኘው ፍልስጤም መዲና ናት ይላሉ።

ኬንያ እአአ 2011 ላይ አል ሸባብን ለመውጋት እና ለሶማሊያ መንግሥት ድጋፍ ለመስጠት ጦሯን ወደ ሶማሊያ ካዘመተች በኋላ በአል ሸባብ ጥርስ ውስጥ ገብታ ቆይታለች።

ወዳ ዘመዶቻቸውን ያጡ ሰዎች ቺሮሞ ተብሎ በሚጠራው የአስክሬን ማቆያ ስፍራ

የፎቶው ባለመብት, Getty Images

የምስሉ መግለጫ, ወዳጅ ዘመዶቻቸውን ያጡ ሰዎች ቺሮሞ ተብሎ በሚጠራው የአስክሬን ማቆያ ስፍራ

ኤኤፍፒ እንደዘገበው፤ ትናንት ከሽብር ጥቃቱ ጋር ግንኙነት ሳይኖራቸው አይቀሩም የተባሉ ሁለት ሰዎች በቁጥጥር ሥር ውለዋል።

በቁጥጥር ሥር ከዋሉት መካከል አንዷ ከአሸባሪዎቹ የአንደኛው ሚስት እንደሆነች ሌላኛው ተጠርጣሪ ደግሞ ለጥቃቱ በገንዘብ ድጋፍ ሳያደርግ አይቀርም ሲሉ የኬንያ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

በሽብር ጥቃቱ የተገደሉት እነማን ናቸው?

የአሜሪካ ዜጋ የሆነው ጄሰን ስፒንድለር ከሟቾቹ መካከል አንዱ ነው። የጄሰን ወንድም የሆነው ጆናተን በትዊተር ገጹ ላይ እንዳስታወቀው ወንድሙ በኒው ዮርክ እአአ 2001 ተፈጽሞ ከነበረውን 9/11 የሽብር ጥቃት በህይወት ተርፎ ነበር።

የ X ይዘትን ይለፉት, 1
ይዘቱን X ይፈቅዳሉ?

ይህ ጽሑፍ በX. የቀረበ ይዘት ይዟል። ገጹ ቴክኖሎጂዎች ወይም ኩኪዎች ሊኖረው ስለሚችል ገጹ ከመከፈቱ በፊት የእርስዎን ፍቃድ እንጠይቃለን። ፍቃድዎን ከመስጠትዎ በፊት የX ኩኪ ፖሊሲ እና የ ማንበብ ይፈልጉ ይሆናል። ይዘቱን ለማንበብ ‘እቀበላለሁ ቀጥል’ የሚለውን ይምረጡ።

ማሳሰቢያ፡ የሦስተኛ ወገን ይዘቶች ማስታወቂያ ሊኖራቸው ይችላል

የ X ይዘት መጨረሻ, 1

Presentational white space

የእንግሊዝ የውጪ ጉዳይ ሚንስትር ቢሮ ከሟቾቹ መካከል ሉክ ፖተር የተሰኘ የእንግሊዝ ዜጋ እንደሚገኝበት አስታወቋል። በተጨማሪም አንድ እንግሊዛዊ በጥቃቱ ጉዳት አጋጥሞታል።

ኬንያዊው እግር ኳስ ተጫዋች ከሟቾቹ መካከል አንዱ ነው። ኮብራ በመባል የሚታወቀው ተጫዋች ለኳስ ባለው ፍቅር በብዙዎች ዘንድ ይታወቃል።

የ X ይዘትን ይለፉት, 2
ይዘቱን X ይፈቅዳሉ?

ይህ ጽሑፍ በX. የቀረበ ይዘት ይዟል። ገጹ ቴክኖሎጂዎች ወይም ኩኪዎች ሊኖረው ስለሚችል ገጹ ከመከፈቱ በፊት የእርስዎን ፍቃድ እንጠይቃለን። ፍቃድዎን ከመስጠትዎ በፊት የX ኩኪ ፖሊሲ እና የ ማንበብ ይፈልጉ ይሆናል። ይዘቱን ለማንበብ ‘እቀበላለሁ ቀጥል’ የሚለውን ይምረጡ።

ማሳሰቢያ፡ የሦስተኛ ወገን ይዘቶች ማስታወቂያ ሊኖራቸው ይችላል

የ X ይዘት መጨረሻ, 2

Presentational white space

የልብ ወዳጆች የሆኑት ኬንያውያኑ አብደላ ዳሂር እና ፋይሰል አህመድ ከሟቾቹ መካከል ይገኙበታል።

አብደላ እና ፋይሰል በሆቴሉ ምሳ እየተመገቡ ሳለ ነበረ የሽብር ጥቃቱ የተፈጸመው። ሁለቱ ጓደኛሞች "ሁሌም የማይነጣጠሉ" ተብለው በሚያውቋቸው ሰዎች አንደበት ይገለጻሉ።