በፊሊፒንስ ጥቁሩን የኢየሱስ ሀውልት ለማክበር በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ አደባባይ ወጡ

ከፍተኛ ቁጥር ያለው ህዝብ ታሪካዊውን ጥቁሩን የኢየሱስን ሀውልት ለማየት በመዲናዋ ማኒላ ተሰባስበዋል።

የፎቶው ባለመብት, AFP

በጣም ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ፊሊፒናውያን ታሪካዊውንና ጥቁሩን የኢየሱስ ሀውልት ለማክበር በመዲናዋ ማኒላ በጎዳናዎች ላይ ወጥተው ነበር።

በዚህ አመታዊ ክብረ በዓል በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ፊሊፒናውያን ታሪካዊውን የናዝሬቱን እየሱስ ሀውልት ለማየት ወደ ጎዳናዎች ይወጣሉ።

ሀውልቱ የተቀረፀው በሜክሲኮ ሲሆን ወደ ፊሊፒንስ የመጣው 17ኛው ክፍለ ዘመን ላይ ነው። በጊዜውም በመርከብ ላይ ከተነሳ እሳት ተርፏል። በፊሊፒንስ የተቀደሰና ከፍተኛ ስፍራ የሚሰጠው ይህ ሀውልት የእየሱስን ስቅለት የሚያሳይ ነው።

የፎቶው ባለመብት, AFP

የምስሉ መግለጫ, ሀውልቱ የተቀረፀው በሜክሲኮ ሲሆን ወደ ፊሊፒንስ የመጣው 17ኛው ክፍለ ዘመን ላይ ነው። በጊዜውም በመርከብ ላይ ከተነሳ እሳት ተርፏል። በፊሊፒንስ የተቀደሰና ከፍተኛ ስፍራ የሚሰጠው ይህ ሀውልት የእየሱስን ስቅለት የሚያሳይ ነው።
ኩያፖ በምትባል የሀገሪቷ ግዛት በሚገኝ ቤተክርስቲያን ውስጥ መስቀሉ የሚቀመጥ ሲሆን፤ በየአመቱ ጥር ወር ላይ ግን የተመረጡ ሰዎች ተሸክመውት በመዲናዋ ማኒላ ለሰባት ኪሎ ሜትር ያህል ጉዞ ይደረጋል።

የፎቶው ባለመብት, EPA

የምስሉ መግለጫ, ኩያፖ በምትባል የሀገሪቷ ግዛት በሚገኝ ቤተክርስቲያን ውስጥ መስቀሉ የሚቀመጥ ሲሆን፤ በየአመቱ ጥር ወር ላይ ግን የተመረጡ ሰዎች ተሸክመውት በመዲናዋ ማኒላ ለሰባት ኪሎ ሜትር ያህል ጉዞ ይደረጋል።
በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ አማኞች የስነ ስቅለቱን ሀውልት ለማየት የሚመጡ ሲሆን፤ ብዙዎችም ባዶ እግራቸውን ናቸው። ሀውልቱን መንካትም ሆነ መጠጋት ከበሽታም እንደሚፈውስና መልካም እድል እንደሚያመጣ ይታመናል።

የፎቶው ባለመብት, Reuters

የምስሉ መግለጫ, በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ አማኞች የስቅለቱን ሀውልት ለማየት የሚመጡ ሲሆን፤ ብዙዎችም ባዶ እግራቸውን ናቸው። ሀውልቱን መንካትም ሆነ መጠጋት ከበሽታም እንደሚፈውስና መልካም እድል እንደሚያመጣ ይታመናል።
በፊሊፒንስ ውስጥ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው አጥባቂ የካቶሊክ አማኞች ያሉ ሲሆን ጥቁሩን የናዝሬቱ እየሱስን ሀውልት ለመንካትም ከፍተኛ አደጋ አይበግራቸውም።

የፎቶው ባለመብት, Reuters

የምስሉ መግለጫ, በፊሊፒንስ ውስጥ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው አጥባቂ የካቶሊክ አማኞች ያሉ ሲሆን የጥቁሩን የናዝሬቱ እየሱስን ሀውልት ለመንካትም ከፍተኛ አደጋ አይበግራቸውም።
የፊሊፒንስ ቀይ መስቀል ድርጅት እንዳሳወቀው አረፋፈዱ ላይ ስድስት መቶ ሰዎች ከመተንፈስ ችግር፣ አቅልን መሳትና ሰውነታቸው ላይ ብዝለት ጋር በተያያዘ ህክምና እንደሰጡ ነው። ሶስት ግለሰቦች ደግሞ ህመማቸው ጠና ያለ በመሆኑ ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል።

የፎቶው ባለመብት, EPA

የምስሉ መግለጫ, የፊሊፒንስ ቀይ መስቀል ድርጅት እንዳሳወቀው አረፋፈዱ ላይ ለስድስት መቶ ሰዎች ከመተንፈስ ችግር፣ አቅልን መሳትና ሰውነታቸው ላይ ብልዘት ጋር በተያያዘ ህክምና እንደሰጡ ነው። ሶስት ግለሰቦች ደግሞ ህመማቸው ጠና ያለ በመሆኑ ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል።
ጉዞው ከመጀመሩ በፊት ሀውልቱ በቤተክርስቲያኗ የሚባረክ ሲሆን ብዙዎችም ከሀውልቱ ጋር የሚመሳሰል የራሳቸውን ሀውልት ለማስባረክ ይዘው ይመጣሉ።

የፎቶው ባለመብት, Getty/TED ALJIBE

የምስሉ መግለጫ, ጉዞው ከመጀመሩ በፊት ሀውልቱ በቤተክርስቲያኗ የሚባረክ ሲሆን ብዙዎችም ከሀውልቱ ጋር የሚመሳሰል የራሳቸውን ሀውልት ለማስባረክ ይዘው ይመጣሉ።
የካቶሊክ እምነት አመራሮች ይህ ሰልፍ የሚያሳየው እምነቱ ምን ያህል እያደገና እየጠነከረ መሆኑን ነው ብለዋል።

የፎቶው ባለመብት, Getty/TED ALJIBE

የምስሉ መግለጫ, የካቶሊክ እምነት አመራሮች ይህ ሰልፍ የሚያሳየው እምነቱ ምን ያህል እያደገና እየጠነከረ መሆኑን ነው ብለዋል።