የላውሮ ግምት፡ አርሴናል ከቶተንሃም እንዲሁም ሊቨርፑል ከኤቨርተን

የፎቶው ባለመብት, Shaun Brooks
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 14ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ሦስት ደርቢዎች ይካሄዳሉ፤ የለንደን እና መርሲ ሳይድ ደረቢ።
ኤምሬትስ ላይ አርሴናል ቶተንሃምን ሲያስተናግድ አንፊልድ ላይ ደግሞ ሊቨርፑል እና ኤቨርተን ይጫወታሉ። ቼልሲ በበኩሉ በሜዳው ፉልሃምን ያስተናግዳል።
የቢቢሲው የእግር ኳስ ተንታኝ ማርክ ላውረንሰን እነዚህን ጨምሮ የሌሎቹንም ጨዋታዎች ግምት አስቀምጧል።
የላውሮ ግምቶች
አርብ

የፎቶው ባለመብት, BBC Sport
ካርዲፍ ከዎልቭስ
ዎልቭሶች ባለፉት አምስት ጨዋታዎች ማግኘት የቻሉት አንድ ነጥብ ብቻ ነው። ከእነዚህ ጨዋታዎች በአንዳንዶቹ ጥሩ መንቀሳቀስ ችለዋል።
ካርዲፎች በበኩላቸው በኤቨርተን 1 ለ 0 ተሸንፈዋል። ኤቨርተኖች ጨዋታውን ማሸነፍ የሚገባቸው ቢሆንም ካርዲፎች ጥሩ ተንቀሳቅሰዋል። ይህን ደግሞ ከዎልቭስ ጋርም ይደግሙታል።
የላውሮ ግምት: 1-1
ቅዳሜ

የፎቶው ባለመብት, BBC Sport
ክሪስታል ፓላስ
ሁለቱም ቡድኖች ከወራጅ ቀጠና ትንሽ ከፍ ያሉ ሲሆን ጎል የማስቆጠር ችግርም አለባቸው።
ፓላሶች ባለፈው ሳምንት ወደ ኦልድትራፎርድ በማቅናት አንድ ነጥብ ማግኘታቸው ጥሩ ሲሆን በዚህ ሳምንት ነጥብ መጣል አይኖርባቸውም።
የላውሮ ግምት: 1-0

የፎቶው ባለመብት, BBC Sport
ሃደርስፊልድ ከብራይተን
ዎልቭስን ካሸነፉት ሃደርስፊልዶች ጋር የሚደረገው ጨዋታ ለብራይተኖች ከባድ ነው።
ሃደርስፊልዶች ካለፉት ደካማ ውጤቶች በኋላ ጥሩ ውጤት ከማስመዝገባቸውም በተጨማሪ ጥሩ እየተንቀሳቀሱ ነው።
የላውሮ ግምት: 1-0

የፎቶው ባለመብት, BBC Sport
ሌስተር ከዋትፎርድ
ሌስተሮች በሜዳቸው ካሸነፉ ወራት ተቆጠሩ።
ዋትፎርዶች ባለፈው ሳምንት በሊቨርፑል በሦስት ጎል መሸነፍ አልነበረባቸውም።
የላውሮ ግምት: 2-0

የፎቶው ባለመብት, BBC Sport
ማንቸስተር ሲቲ ከበርንማውዝ
በርንማውዞች ከሦስት ሽንፈት በኋላ ከማንቸስተር ሲቲ ጋር በሚያደርጉት ጨዋታም የተለየ ውጤት አይጠብቁም።
ስለድል ማሰብ ያለባቸው ከዚህ ሳምንት በኋላ ነው። ምክንያቱም ብዙ ቡድኖች ከማንቸስተር ሲቲ ጋር ሲጫወቱ የሚያስቡት በዚህ መልኩ ነው።
የላውሮ ግምት: 3-0

የፎቶው ባለመብት, BBC Sport
ኒውካስል ከዌስት ሃም
ኒውካስሉ አሰልጣኝ ራፋኤል ቤኒቴዝ ጥሩ ውጤት ማስመዝገብ ሲጀምሩ ለብዙ ጨዋታዎች ነው። ባለፉት አራት ጨዋታዎችም አልተሸነፉም።
ዌስት ሃሞች ደግሞ ከስድስት ጨዋታዎች አንዱን ብቻ ነው ያሸነፉት። አቋማቸው የሚዋዥቅ ቡድን ቢሆንም ወደ ወራጅ ቀጠና ይገባሉ ብዬ አላምንም።
የላውሮ ግምት: 2-0

የፎቶው ባለመብት, BBC Sport
ሳውዝሃምፕተን ከማንቸስተር ዩናይተድ
ሳውዝሃምፕተኖች ውጤታማ መሆን እየቻሉ አይደለም። ማንቸስተር ዩናይትዶችም ቢሆኑ ጥሩ ባይሆኑም በዚህ ጨዋታ ግን የበላይ ይሆናሉ።
ከክሪስታል ፓላስ እና ያንግ ቦይስ ጋር እንዳየነው ዩናይትዶች በአጥቂ መስመር ችግር አለባቸው። ሆኖም ይህን ጨዋታ እንደሚያሸንፉ እገምታለሁ።
የላውሮ ግምት: 0-2
እሑድ

የፎቶው ባለመብት, BBC Sport
ቼልሲ ከፉልሃም
አዲሱ የፉልሃም አሰልጣኝ በመጀመሪያ ጨዋታቸው ድል ቢያስመዘግቡም ይኼኛው ግን ከባድ ይሆንባቸዋል።
እንደገመትኩትም ቼልሲዎች ባለፈው ሳምንት ወደ ቶተንሃም በማቅናት የመጀመሪያ ሽንፈታቸውን አስተናግደዋል። ሆኖም ተከታታይ ሽንፈት ወይም ውጤት ማጣት ይገጥማቸዋል ብዬ አላስብም።
የላውሮ ግምት: 2-0

የፎቶው ባለመብት, BBC Sport
አርሴናል ከቶተንሃም
ቶተንሃሞች ባለፉት ሁለት ሳምንታት በሊጉም ሆነ በአውሮፓ ደረጃ ከባድ ጨዋታዎች ቢገጥሟቸውም ሁሉንም አሸንፈዋል። ከዚህ በተጨማሪ የተጫዋቾች ከጉዳት መመለስና ማገገም ይህን ጨዋታ ያሸንፋሉ እንድል አድርጎኛል።
አርሴናሎች ባለፉት ጨዋታዎች አላሳመኑኝም። ሆኖም ባለፉት 18 ጨዋታዎች ሳይሸነፉ ለመጓዝ ችለዋል።
የላውሮ ግምት: 1-2

የፎቶው ባለመብት, BBC Sport
ሊቨርፑል ከኤቨርተን
ኤቨርተኖች በአሰልጣኝ ማርኮ ሲልቫ ስር ጠንካራ በመሆን ላይ የሚገኙ ሲሆን መጀመሪያ የመርሲ ሳይድ ደርቢያቸው ግን ከባድ ፈተና ነው።
ሊቨርፑሎች በሊጉ አናት ላይ ከማንቸስተር ሲቲ ላለመራቅ ኤቨርተኖች ደግሞ እስከአራት ያለውን ደረጃ ለመያዝ የሚያደርጉት ጨዋታ ከባድ ይሆናል።
የላውሮ ግምት: 2-0












