የነጻነት ቅርጫት፡ ማሕበራዊ ሚዲያ

ዛሬ ላይ በዓለማችን ላይ ከሚኖረው የሰው ልጅ መካከል ግማሽ ያህሉ እንደ ፌስቡክ እና ትዊተር የመሳሰሉ ማሕበራዊ ሚዲያዎችን ይጠቀማል።
በምራብ እና ሰሜን አውሮፓ ደግሞ ከ10 ሰዎች አንዱ ቢያስ አንድ የማሕበራዊ ሚዲያ ኔትወርክ ተጠቃሚ ነው።
በማሕበራዊ ሚዲያ ላይ የተጓደኘናቸውን ወዳጆቻችንን አልያም ከምንከተላቸው ታዋቂ ግለሰቦችን ጋር የእራሳችንን ህይወት የምናነጻጽር ከሆና ምናልባትም እራሳችንን ችግር ውስጥ እየከተትን ሊሆን ይችላል።
የጥናት ውጤቶች እንደሚያሳዩት፤ የማሕበራዊ ሚዲያ አብዝተው የሚጠቀሙ ግለሰቦች በአዕምሮ ህመም መጠቃታቸውን ሪፖርት የማድረጋቸው አጋጣሚ ከፍተኛ ነው።
በተለየ መልኩ ወጣት ሴቶች ማሕበራዊ ሚዲያው ስለ መልካቸው አብዝተው እንዲጨነቁ እንደሚያደርጋቸው ይናገራሉ። ገርልጋይዲንግ የተባለ ድርጅት ያካሄደው ጥናት እንደጠቆመው፤ ዕድሜያቸው ከ7-10 የሆኑ ታዳጊ ሴቶች የማሕበራዊ ሚዲያ በሚጠቀሙበት ወቅት ዋናው የሚያሳስባቸው ጉዳይ የመልካቸው ነገር ነው። በጥናቱ ከተካተቱት ሲሶው እንከን የለሽ የሆነ መልክ ኖሮን መታየት እንሻለን ብለዋል።
በሌላ በኩል ስለ ማሕበራዊ ሚዲያ በጎ አስተያየት የሚሰጡ በርካቶች አሉ። ማሕበራዊ ሚዲያው ሰዎች የተሰማቸውን እንዲገልጹ እና ውይይት እንዲያደርጉ እድል ይሰጣል ይላሉ።











