የነጻነት ቅርጫት፡ የጋብቻ ቀለበቶች

በቀደመው ጊዜ ትዳር ይመሰረት የነበረው ለጎሳ እና ፖለቲካዊ ቁርኝነት ትርፍ ነበር። አሁን ግን በአብዛኛው ትዳር የሚመሰረተው ውድ የሰርግ ስነ-ስርዓትን ተከትሎ በፍቅር ላይ በመመርኮዝ ነው።
ለምሳሌ በእንግሊዝ ሃገር በአማካይ የአንድ የሰርግ ወጪ 39ሺህ ዶላር (ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ) ያስወጣል።
ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በአደጉ ሃገራት አዲስ የሚጋቡ ጥንዶች ቁጥር እየቀነሰ ሲሆን በተቃራኒው ጋብቻቸውን የሚያፈርሱ ጥንዶች ቁጥር እየጨመረ ነው። ለጋብቻ ቁጥር መቀነስ እንደምክንያትነት ከሚጠቀሱ ጉዳዮች መካከል ትደር ለመመስረት እና ሰርግ ለመደገስ የሚያስፈልገው ከፍተኛ ወጪ ነው።











