የአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ፅህፈት ቤት ሀላፊ ማርክ ሚዶውስ በኮሮና ተያዙ
የአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ፅህፈት ቤት ሀላፊ ማርክ ሚዶውስ የኮቪድ-19 ምርመራ አድርገው ቫይረሱ እንደተገኘባቸው ባለስልጣናት ለአሜሪካ መገናኛ ብዙሃን ገለጹ፡፡
የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ሳያደርጉ ሕዝብ በሚሰበሰብባቸው ዝግጅቶች ላይ ብዙ ጊዜ የሚታዩት ሚዶውስ እንዴት ቫይረሱ እንደያዛቸው ግልጽ አልሆነም፡፡
ኃላፊው በትራምፕ አስተዳደር ውስጥ ከሚሠሩ እና በቫይረሱ ከተያዙ ሰዎች መካከል አንደሱ ሲሆኑ በአሜሪካ 230,ሺህ የሚሆኑ ሰዎች በቫይረሱ ምክንያት ህይወታቸው አልፏል፡፡
አሜሪካ አርብ ከ127 ሺህ በላይ አዲስ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን ያስመዘገበች ሲሆን ይህም ለሦስተኛ ተከታታይ ቀናት ዕለታዊ ክብረወሰን ሆኖ ተመዝግቧል፡፡
የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ በአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ቁልፍ ርዕስ የነበረ ሲሆን ሰዎች ድምጻቸውን በፖስታ እና ቀደም ብለው በአካል እንዲሰጡ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡
ከቀናት በፊት ሚዶውስ ከሲኤንኤን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ አሜሪካ "ወረርሽኙን ለመቆጣጠር አትችልም" ያሉ ሲሆን ኮቪድ-19 ማሸነፍ የሚቻለው በክትባት እና ህክምና ብቻ እንደሆነ አስታውቀዋል።
ሙሉውን ለማንበብ፦የአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ፅህፈት ቤት ሀላፊ ማርክ ሚዶውስ በኮሮና ተያዙ



















