ሁለተኛው የዶናልድ ትራምፕ የሥልጣን ዘመን ምን ሊመስል ይችላል?

ለአንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች የዶናልድ ትራምፕ የመጀመሪያው የሥልጣን ዘመን በሁለተኛው ዙር እንዴት ሊሆን እንደሚችል ጥሩ ማሳያ ሆኖ ሊቀርብ ይችላል ይላሉ።

ዶናልድ ትራምፕ አሁን ሥልጣን መልሰው ሲጨብጡ በመጀመሪያው የፕሬዝዳንትነት ዘመናቸው ዕቅዳቸውን ተግባራዊ ማድረግ ካቆሙበት እንደሚቀጥሉ ብዙዎች ያምናሉ።

አንደኛው ያልተጠናቀቀው ፕሮጀክት የአሜሪካን ደቡባዊ ድንበርን መዝጋት እና የድንበር አጥር ግንባታ ግንባታን ማጠናቀቅ ነው። ይህ የመጀመሪያው ዙር የሥልጣን ዘመናቸው ማሳያ ነው። የድንበር አጥሩን ለመገንባት የሚያስፈልገውን ገንዘብ የአገሪቱ ኮንግረስ አልፈቀደላቸውም።

ግንባታውን በማጠናቀቅ በምርጫ ዘመቻ ወቅት የገቡትን ቃል ይጠብቃሉ ተብሎ ይገመታል።

ስደተኞችን በጅምላ ማባረር

ፕሬዝዳንት ትራምፕ በአገሪቱ ውስጥ ለመኖር ሕጋዊ ፍቃድ የሌላቸውን ሰዎች በጅምላ ለማባረር ያላቸውን ዕቅድ ለማሳካት የኮንግረሱን ድጋፍ ሊፈልጉ ይችላሉ።

በፒው የምርምር ማዕከል ግምት መሠረት እአአ በ2022 ብቻ 11 ሚሊዮን ያህል ሕገ ወጥ ስደተኞች በአሜሪካ ውስጥ ነበሩ። ትራምፕ እና ደጋፊዎቻቸው ቁጥሩ ከዚህም እንደሚልቅ ተናግረዋል።

ስደተኞችን በጅምላ ማባረር ብዙ ወጪ የሚጠይቅ እና ተግባራዊ ለማድረግም አስቸጋሪ ይሆናል በሚል ባለሙያዎች እያስጠነቀቁ ይገኛሉ። ሰነድ አልባ የጉልበት ሠራተኞች ቁልፍ ሚና በሚጫወቱባቸው አንዳንድ የኢኮኖሚ ዘርፎች ላይ አሉታዊ ተጽእኖ እንደሚያሳድርም ገልጸዋል።

ዶናልድ ትራምፕ በሐምሌ ወር የሪፐብሊካን ፓርቲ ፕሬዝዳንታዊ ዕጩ ሲሆኑ “አስከፊውን የዋጋ ንረት ቀውስ በአስቸኳይ ለማስቆም፣ የወለድ ምጣኔን ለማውረድ እና የኃይል ወጪን ለመቀነስ” ቃል ገብተዋል።

በሚቀጥለው ዓመት የሚያበቃውን እና እአአ በ 2017 ያስተዋወቁትን ቅነሳ ማራዘም ይፈልጋሉ። ይህም የታክስ ሕጉን በማቃለል ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን እና ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋት ያለመ ትልቁ የታክስ ማሻሻያ ነው።

ትልቁ ቅነሳ የሚደረገው ለንግድ ድርጅቶች እና ለሐብታሞች ነበር። ይህም እንዲቀለበስ ዴሞክራቶች ደጋግመው ጠይቀዋል።

ትራምፕ የኮርፖሬት ተመኖችን የበለጠ በመቀነስ ወደ 15 በመቶ ዝቅ እንደሚያደርጉ እና ለጡረተኞች በሚሰጡት ድጋፎች እና የማኅበራዊ ዋስትና ክፍያዎች ላይ ታክስን ያስወግዳሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ሌላ የንግድ ጦርነት?

ከፍተኛ የነዳጅ ዋጋ መናሩ ለዋጋ ግሽበት አስተዋጽኦ አድርጓል ብለው ስለሚያምኑ ተጨማሪ ነዳጅ ለማውጣት ወደ ቁፈራ ፊታቸውን ያዞራሉ። ይህንን ማድረጉ የኃይል ወጪን ቢቀንስም ተንታኞች ግን ጥርጣሬ አላቸው።

ከውጭ በሚገቡ ምርቶች ላይ ከ10 እስከ 20 በመቶ ታሪፍ ለመጫንም አስበዋል። ትልቁ ታሪፍ 60 በመቶ ሲሆን፣ በቻይና ምርቶች ላይ የሚጣል ይሆናል። ብዙ ኢኮኖሚስቶች ግን እንዲህ ዓይነት እርምጃዎች የአሜሪካ ሸማቾች ላይ ከፍተኛ የዋጋ ውድነትን ይፈጥራል በሚል አስጠንቅቀዋል።

ፕሬዝዳንት ትራምፕ በመጀመሪያ የሥልጣን ዘመናቸው ቻይናን ኢ-ፍትሃዊ የንግድ አሠራር እና የአዕምሯዊ ንብረት ስርቆትን ታካሂዳለች በማለት በመወንጀል ከቤይጂንግ ጋር የንግድ ጦርነት ጀምረዋል።

የአሜሪካ ኮንግረስ የሚኖረው ቅርጽ ፖሊሲዎቹን በሚፈልጉት መንገድ ማስኬድ ይችሉ እንደሆነ ይወስናል።

ከ2017 እስከ 2019 ባሉት ዓመታት ሪፐብሊካኖች በሴኔት እና በእንደራሴዎች ምክር ቤት ላይ የበላይነት እንደነበራቸው ልብ ሊባል ይገባል።

መጀመሪያ ላይ ትራምፕ ከኮንግረሱ አሠራር ጋር ብዙም አለመዋሃዳቸው ይታይ ነበር። ይህም ሪፐብሊካኖች በዋይት ሐውስ እና በኮንግረስ ያላቸውን ብላጫ እንዳይጠቀሙ እንቅፋት ሆኖባቸው ነበር ሲሉ የፖለቲካ ተንታኞች በወቅቱ ተናግረዋል።

[ማስታወሻ፡ በሴኔት እና በምክር ቤት ውጤቶች ላይ በመመስረት ከታች ካሉት አንዱን ይጠቀሙ]

አማራጭ አንድ፡ ሪፐብሊካኖች በምርጫው ሁለቱን ምክር ቤቶች መቆጣጠር ከቻሉ የትራምፕ አስተዳደር የድንበር ደኅንነትን፣ የድንበር አጥርን ማጠናቀቅ እና የግብር ቅነሳን ጨምሮ የገንዘብ ድጋፍን የሚያጠቃልለውን ሕግ ሊከተሉ ይችላሉ።

አማራጭ ሁለት፡ ሪፐብሊካኖች በምርጫው በሴኔት ወይም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ብቻ ካሸነፉ የትራምፕ አስተዳደር የድንበር ደኅንነት፣ የድንበር አጥሩን የማጠናቀቂያ ገንዘብ ለማግኘት እና የግብር ቅነሳ ለማድረግ በራሳቸው መንገድ ይንቀሳቀሳሉ።

አማራጭ ሦስት፡ ሪፐብሊካኖች በምርጫው ሁለቱንም ምክር ቤቶች ካላሳኩ የትራምፕ አስተዳደር የድንበር ደኅንነትን፣ የድንበር አጥር ማጠናቀቅን እና የግብር ቅነሳን ጨምሮ ሌሎች ሥራዎችን ለማከናወን የሚረዳቸውን ገንዘብ ለማግኘት ሌላ መንገድ መፈለግ ይኖርባቸዋል።

ጽንስ ማቋረጥ ማገድ

ትራምፕ በመጀመሪያ የሥልጣን ዘመናቸው የ1973ቱን የጽንስ ማቋረጥ ሕገ መንግሥታዊ መብት ለመሻር ወሳኝ የሆኑትን ሦስት የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞችን ሹመት አጽድቀዋል። ፕሬዝዳንቱ በሁለተኛው የሥልጣን ዘመናቸው ምን ሊያደርጉ እንደሚችሉ ብዙዎች ከወዲሁ እያሰቡ ነው።

በመስከረም ወር ከካማላ ሃሪስ ጋር ባደረጉት የምርጫ ክርክር የፌደራል ጽንስ ማቋረጥ እገዳን እንደማይፈርሙ ተናግረዋል። “እገዳውን የምንፈርምበት ምንም ምክንያት የለም ምክንያቱም ሁላችንም የሚፈልገውን አግኝተናል” ብለዋል።

“ገለልተኝነት”

በውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ረገድ የፕሬዝዳንት ትራምፕ ሁለተኛ የሥልጣን ዘመን የመጀመሪያቸውን ሊመስል ይችላል። በዚህም ከሌሎች የዓለም አካባቢ ግጭቶች አሜሪካን የሚያርቅ ነው።

ከሩሲያ ጋር በሚደረግ ድርድር በዩክሬን ያለውን ጦርነት “በ24 ሰዓት ውስጥ” እንደሚያስቆሙ ተናግረዋል። ይህ እርምጃ የሩሲያውን ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲንን ያገዝፋል ሲሉ ዴሞክራቶች ተችተውታል።

ትራምፕ ራሳቸውን የእስራኤል ጠንካራ ደጋፊ አድርገው ቢገልጹም፣ በጋዛ ያለውን ጦርነት እንዴት እንደሚያስቆሙ ግን ብዙም አልተናገሩም።

“የትራምፕን የፕሬዝዳንትነት ጊዜ በብቸኝነት እና በወገንተኝነት ይገለጻል” ሲሉ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ ጉዳዮች እና የአደጋ ጊዜ እርዳታ ምክትል ዋና ፀሐፊ የነበሩት ማርቲን ግሪፍትስ ተናግረዋል።

የቀድሞ የኔቶ ኃላፊ እና በኤክሰተር ዩኒቨርሲቲ የስትራቴጂ እና ደኅንነት ፕሮፌሰር የሆኑት ጄሚ ሺአ በበኩላቸው የፕሬዝዳንት ትራምፕ የመጀመሪያ የሥልጣን ዘመን ረብሻ የነበረ ቢሆንም “ቀጣይነት ነበረው” ብለዋል።

“ከኔቶ አባልነት አልወጣም። የአሜሪካ ወታደሮችን ከአውሮፓ አላስወጣም። ለዩክሬን የጦር መሳሪያዎችን የሰጠ የመጀመሪያው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ነበር” ሲሉ አክለዋል።

ዶናልድ ትራምፕ በአገሪቱ ታሪክ ተከታታይ ላልሆነ ጊዜ ለሁለተኛ የሥልጣን ዘመን የተመረጡ ሁለተኛው ፕሬዝዳንት ናቸው።

የመጀመሪያው ግሮቨር ክሊቭላንድ ናቸው። እአአ ከ1885 እስከ 1889 በፕሬዝዳንትነት ካገለገሉ በኋላ በቀጣዩ ምርጫ ተሸንፈዋል። ለሁለተኛ ጊዜ በመመረጥ ከ1893 እና 1897 በፕሬዝዳንትነት በድጋሚ አገልግለዋል።