የግብፅ መካነ መቃብር፡ ሳቃራ ፒራሚድ ኮምፕሌክስ አቅራቢያ አዲስ ግኝት ይፋ ተደርጓል

የፎቶው ባለመብት, AFP/Getty Images
በግብፅ ቄሶች ያረፉበትና ላለፉት 4400 ዓመታት ተነክቶ የማያውቅ መካነ መቃብር ማግኘታቸውን አርኪዮሎጂስቶች አስታወቁ።
በግብፅ የአንቲኪዩቲስ ምክር ቤት ዋና ፀሃፊ የሆኑት ሙስጠፋ ዋዚሪ ባለፉት አስርት ዓመታት ታይቶ የማይታወቅ አስደናቂ ግኝት ነው ሲሉ ገልፀውታል።
በካይሮ አቅራቢያ ሳቃራ ፒራሚድ የተገኘው ይህ መካነ መቃብር በቀለማት ያሸበረቁ ሥዕላዊ መግለጫዎች፣ የፈርኦን ሐውልቶች እንዲሁም ዋህትይ የተባሉት የንጉሣዊ ቄስ ከእናታቸው፣ ከሚስታቸው እና ከዘመዶቻቸው ጋር በሚያሳይ ምስል የተሞላ ነው።
አርኪዮሎጂስቶች የመካነ መቃብሩ ባለቤት የመቃብር ክዳን ማግኘታቸውን ተከትሎ ሌሎች አዳዲስ ግኝቶችን ለመፈለግ በአውሮፓውያኑ ታህሳስ 16 ቁፋሮ መጀመራቸው ታውቋል።

የፎቶው ባለመብት, AFP/Getty Images

የፎቶው ባለመብት, AFP/Getty Images

የፎቶው ባለመብት, AFP/Getty Images

የፎቶው ባለመብት, Reuters

የፎቶው ባለመብት, Reuters

የፎቶው ባለመብት, Reuters

የፎቶው ባለመብት, EPA

የፎቶው ባለመብት, Reuters

የፎቶው ባለመብት, EPA

የፎቶው ባለመብት, Reuters








