የቺቦክ ማስታወሻ ደብተሮች ፡ የቦኮ ሃራም እገታ የጽሑፍ ቅጂዎች

ሞተር ሊሰርቁ መጥተው የነበሩት የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች የፈለጉትን ሲያጡ የነበሩትን ወደ 200 ገደማ ልጃገረዶች አገተው ወደ ሳምቢሳ ይዘዋቸው ለሜሄድ ወሰኑ... ከዚያስ?

አንዳንዶቹ ሴቶች በታጣቂዎቹ መኪኖች ላይ ተጭነው ብዙዎቹ ደግሞ ሽጉጥ ተደቅኖባቸው ብዙ ኪሎሜትሮችን ከተራመዱ በኃላ የጭነት መኪኖች መጥተው አፈሷቸው።

Presentational grey line

ማስታወሻ ደብተሮቹን ማን ጻፋቸው?

የማስታወሻ ደብተሮቹ
  • ዋና ጸሐፊዎቹ ፡ ናዖሚ አዳሙ እና ሣራ ሳሙኤል
  • ሮዳ ፒተር፣ ሳራቱ አዩባ እና ማርጋሬት ያማ አነስተኛ አስተዋጽዎችን አበርከተዋል
  • ከመካከላቸው አራቱ ከብዙ ድርድሮች በኃላ በግንቦት 2009 ተለቀዋል
  • ሣራ ሳሙኤል ባለፈው ዓመት ውስጥ አንዱን ታጣቂ ለማግባት ተስማምታ እስካሁን በእገታ ሥር ናት።

የእገታውን ማስታወሻ የመጀመሪያ ክፍል ለማግኘት ይህን ይጫኑ

Presentational grey line

ወደ ቦኮ ሃራም መደበቂያ ደን እያመሩ ሳለ አንዳንድ ተማሪዎች ከጭነት መኪኖቹ እየዘለሉ መውረድ ጀመሩ ግን አንደኛዋ ልጅ ለአንደኛው አጋች ነገረችው።

ድንገት ብቻዋን ትቀራለች ብላ ፈርታ ወይም ሥልጣንን ለማክበር ወይም ደግሞ በስቃይ ብቸኛ ላለመሆን ሊሆን ይችላል።

"መኪናው ውስጥ የነበረችው አንደኛዋ ልጅ 'ሹፌር አንዳንድ ሴቶች ለማምለጥ እየዘለሉ ነው' አለችው። ሹፌሩም በሩን ከፈተና በእጅ መብራት ቢፈልጋቸውም ማንንም ማየት አልቻለም። ስለዚህ አንድ ቦታ ይንቀሳቀሱ መቀመጥ እንዳለባቸው ተናገሩ። ካሁን ወዲህ እሷም ሆነች ማንም ሲዘል ቢያዝ በሽጉጥ እንገልሻለን"።አለ አሽከርካሪው። ከዚያስ...?