ኢራን በጦርነቱ እስካሁን 270 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ውድመት እንደደረሰባት ገለጸች

የፎቶው ባለመብት, Getty Images
ኢራን በጦርነቱ ምክንያት የደረሰባትን ውድመት ግምት ውስጥ በማስገባት የካሳ ክፍያን የድርድሩ አካል ለማድረግ በማሰብ የጉዳቱን መጠን ማስላት መጀመሯን ከአብዮታዊ ዘብ ጋር ግንኙነት ያለው ታስኒም የዜና ወኪል ዘገበ።
የኢራን መንግሥት ቃል አቀባይ ፋቴሜህ ሞሃጀራኒ ለሩሲያ መገናኛ ብዙኃን እስራኤል እና አሜሪካ ከየካቲት 21 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ለ40ቀናት በዘለቀው ጥቃታቸው ያደረሱት ውድመት "ቅድመ ግምት" 270 ቢሊዮን ዶላር አካባቢ መሆኑን ጠቅሰው ይህ ቁጥር ግን ሊለወጥ እንደሚችል ተናግረዋል።
በኢራን የሚገኙ ባለሥልጣናት የደረሰውን ውድመት እያሰሉ መሆኑን የተናገሩት ባለሥልጣኗ ይህም በሕንፃዎች ላይ የደረሰውን ጉዳት እና ኢንዱስትሪዎች ሥራ በማቆማቸው ምክንያት የሚደርሰውን ኪሳራ ያካትታል ማለታቸውን ታስኒም ዘግቧል።
ሞሃጀራኒ ለኢራን መንግሥት መገናኛ ብዙኃን፣ ኢርና ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ከአሜሪካ ጋር በተደረገው ውይይት ከተነሱት ጉዳዮች አንዱ ካሳ መሆኑን ተናግረዋል።
የአሜሪካ ምክትል ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ ቀደም ሲል በፓኪስታን በተካሄደው ውይይት ላይ "ጠቃሚ ውይይቶች" እንደተደረጉ ቢናገሩም ምንም ዓይነት ስምምነት ላይ ግን አልተደረሰም።

የፎቶው ባለመብት, Getty Images



















