በቢሾፍቱ ስለሚገነባው ግዙፍ የአውሮፕላን ማረፊያ አንዳንድ እውነታዎች
በቢሾፍቱ ስለሚገነባው ግዙፍ የአውሮፕላን ማረፊያ አንዳንድ እውነታዎች
የሚያስተናግዳቸው መንገደኞች ቁጥር በፍጥነት እየጨመረ የመጣው የአፍሪካ ግዙፉ አየር መንገድ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ አሉ ከሚባሉ አየር ማረፊያዎች የዋነኛው ይሆናል የተባለውን ግንባታ በሚቀጥለው ዓመት ያስጀምራል።
የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈፋሚ አቶ መስፍን ጣሰው ለቢቢሲ እንደተናገሩት ለዚሁ ሥራ የሚያስፈልገውን ዝግጅት የሚያደርጉ ሰባት የግንባታ ኩባንያዎች ሥራ ጀምረዋል።
በሁለት ምዕራፍ ተከፍሎ ግንባታው የሚካሄደው አየር ማረፊያው በመጀመሪያ ዙር ግንባታው በዓመት 60 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ይኖረዋል።



