እስራኤል በሦስት ወራት ጥቃት የገደለቻቸው የሂዝቦላህ ቁልፍ መሪዎች

የተንቀሳቃሹ ምስል መግለጫ,
እስራኤል በሦስት ወራት ጥቃት የገደለቻቸው የሂዝቦላህ ቁልፍ መሪዎች

ከጥቂት ወራት በፊት በሊባኖሱ ታጣቂ ቡድን ሄዝቦላህ ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት ከፍታ ጦርነት ስታካሂድ የነበረችው እስራኤል በአማሪካ አማካይነት በተደረሰ ስምምነት ተኩስ አቁም መደረሱ ተነግሯል።

በተለይ ከመስከረም ወዲህ በሊባኖስ ላይ በፈጸመቻቸው ጥቃቶች በዋናነት የሄዝቦላህ ከፍተኛ መሪዎችን ዒላማ አድርጋ በርካቶቹን ገድላለች።

በዚህም ከቡድኑ መሪ ሐሳን ናስራላህ በተጨማሪ ሌሎችም የሄዝቦላህ ከፍተኛ ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ አዛዦች ባለፉት ሦስት ወራት በእስራኤል ተገድለዋል። ከእነዚህ መካከል ቁልፍ የሚባሉት እነ ማን ናቸው?