የጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ 100 ቀናት

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ኢትዮጵያን መምራት ከጀመሩበት ዕለት አንስቶ በረካታ ነገሮችን አከናውነዋል። እኛ ቀጣዮቹን ወሳኝ ያልናቸውን 14 ኩነቶች መርጠናል።

2018

  • ኤፕሪል 2 2018, 1 ቀን በሥራ ገበታ ላይ
    ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ቃለ መሀላ ሲፈጽሙ

    ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢህአዴግ ሊቀ መንበር ከሆኑ ከሳምንት በኋላ በሕዝብ እንደራሴዎች ፊት ቃለ መሀላ ፈጸሙ። በእለቱ ስለ ህብረትና ለውጥ ተናግረዋል።

  • ኤፕሪል 28 2018, 27 ቀን በሥራ ገበታ ላይ
    ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለሲዳማ የሀገር ሽማግሌዎች ሰላምታ ሲሰጡ

    ሥልጣን ይዘው ብዙም ሳይቆይ በክልል ከተሞች እየተዘዋወሩ ነዋሪዎችን ማነጋገር ያዙ። በደቡብ ክልል ሀዋሳ ከተማ ተገኝተው የጠቅላይ ሚኒስትር የስልጣን ዘመን ከአስር አመት እንደማይዘል አሳውቀዋል።

  • ኤፕሪል 29 2018, 28 ቀን በሥራ ገበታ ላይ
    የጅቡቲ ፕሬዚዳንት (በስተግራ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ (በስተቀኝ)

    ከሀገር ውጪ መጀመሪያ ያቀኑት ወደ ጅቡቲ ሲሆን ከጅቡቲው አቻቸው ጋር ስለ ኢኮኖሚያዊ ትስስርና የቀጠናው ሰላም ተወያይተዋል። ኢትዮጵያውያን ታራሚዎችንም ከጅቡቲ አስፈትተዋል።

  • ሜይ 29 2018, 28 ቀን በሥራ ገበታ ላይ
    ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (በስተቀኝ) ከአንዳርጋቸው ጽጌ ጋር ሲጨባበጡ (በስተግራ)

    እንግሊዛዊ ዜግነት ያላቸው የግንቦት 7 መሪ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የሞት ፍርዳቸው ተሽሮ ከእስር ተለቀቁ። በተለቀቁ ማግስት በብሔራዊ ቤተ መንግስት ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ተገናኙ።

  • ሜይ 18 2018, 47 ቀን በሥራ ገበታ ላይ
    ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (በስተግራ) ልዑል መሀመድ ቢን ሰልማን አብዱል (በስተቀኝ)

    ከአፍሪካ ውጪ ባደረጉት የመጀመሪያ ጉብኝት ወደ ሳውዲ አረቢያ አምርተው ለሁለት ቀናት በሁለትዮሽ ጉዳዮች እንዲሁም በአለም አቀፍ ሁነቶት ከልዑል መሀመድ ቢን ሰልማን አብዱል ጋር ተወያይተዋል። ጉብኝታቸውን ተከትሎ ከ1000 በላይ ኢትዮጵያውያን ታራሚዎች ከእስር ተለቀዋል።

  • ጁን 4 2018, 64 ቀን በሥራ ገበታ ላይ
    የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በውይይት ላይ

    የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለስድስት ወራት የተደነገገውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አነሳ። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ይነሳል ከተባለበት ግዜ ሁለት ወራት ቀድሞ የተነሳው በሀገሪቱ ሰላምና መረጋጋት በመስፈኑ ነው ተብሏል።

  • ጁን 6 2018, 66 ቀን በሥራ ገበታ ላይ
    የኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት በስብሰባ ላይ

    ገዢው ፓርቲ በመንግስት ባለቤትነት ስር የነበሩትን ቴሌ ኮሙኑኬሽንና አየር መንገድን ለሀገር ውስጥ እና ለውጭ ባለሀብቶች በከፊል ለመሸጥ መወሰኑ ዋነኛ የፖሊሲ ለውጥ ነበር። በሥራ አስፈፃሚው መግለጫ መሰረት ይህ ውሳኔ ያስፈለገው የሀገሪቱን ፈጣን እድገት ለማስቀጠል ነው። በዚሁ ዕለት ነበር የአልጀርሱን ስምምነት ሙሉ በሙሉ ለመተግበር የተወሰነው።

  • ጁን 7 2018, 67 ቀን በሥራ ገበታ ላይ
    የቀድሞ የመከላከያ ኢታማዦር ሹም ሳሞራ የኑስ

    ጠቅላይ ሚኒሰትሩ በጀነራል ሳሞራ የኑስ ምትክ ጀነራል ሰአረ መኮንንን የመከላከያ አዛዥ አድርገዋል። የፀጥታና ደህንነት ኃላፊው አቶ ጌታቸው አሰፋም በአቶ አደም መሀመድ ተተክተዋል።

  • ጁን 9 2018, 69 ቀን በሥራ ገበታ ላይ
    ጠቅላይ ሚኒሰትር ዐብይ አህመድ (በስተግራ) ዩዌሪ ሙሴቪኒ (በስተቀኝ)

    ጠቅላይ ሚኒሰትር ዐብይ አህመድ የኡጋንዳን ከፍተኛውን ሜዳሊያ ተሸልመው በሚቀጥለው ቀን ወደ ግብፅ ተጉዘው የግብፅ አቻቸውን ያገኙ ሲሆን ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱም ከግብፅ የተለቀቁ ታራሚዎችን እንዲሁም የኦነግ አመራር አባላትን ይዘው ተመልሰዋል።

  • ጁን 18 2018, 78 ቀን በሥራ ገበታ ላይ
    እጅና እግሩ በአንድነት የታሰረ ሰው ንድፍ

    ጠቅላይ ሚኒሰትሩ መንግሥት የፖለቲከኛ እስረኞችን ያሰቃይ እንደነበር ይህም ህገ መንግስታዊ እንዳልሆነ ገልፀዋል። ‘ ማሰርና ማሰቃየት ኢ-ህገመንግስታዊ ነው። ሽብርተኝነት ህገ መንግስቱ ከሚፈቅደው ውጭ ስልጣን ላይ ለመቆየት የሚደረግ እርምጃንም ይጨምራል' ብለዋል።

  • ጁን 23 2018, 83 ቀን በሥራ ገበታ ላይ
    የቀይ መስቀል አባላት የተጎዱትን ሲያክሙ

    ቅዳሜ ሰኔ 16 በመስቀል አደባባይ ለድጋፍ በወጡ ሰልፈኞች ላይ በደረሰ የቦንብ ፍንዳታ ሁለት ሰዎች ሞተዋል። ከፍንዳታው በኋላ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥቃቱ የእለቱን ስሜት ለማጠልሸት የተቀነባበረ ነው ብለዋል።

  • ጁን 26 2018, 86 ቀን በሥራ ገበታ ላይ
    ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ የኤርትራን ልዑካን ሲቀበሉ

    የኤርትራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን አባላት አዲስ አበባ ሲደርሱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አቀባበል አድርገውላቸዋል። ኢትዮጵያና ኤርትላ ላለፉት 20 ዓመታት አለመግባባት ውስጥ ቆይተዋል። እንደ ኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከሆነ የሁለቱ ሀገራት መሪዎች በቅርቡ ይገናኛሉ።

  • ጁላይ 5 2018, 97 ቀን በሥራ ገበታ ላይ
    በሽብርተኛነት ተፈርጆ የነበረው ኦነግ ባንዲራ በመስቀል አደባባይ ከፍ ብሎ ሲውለበለብ

    የሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት አባላት በሽብርተኝነት ተፈርጀው የነበሩትን ኦነግ፣ ኦብነግ እና ግንቦት 7 ሽብርተኞች አይደሉም በማለት ከሽብርተኛ ድርጅቶች ዝርዝር አውጥቷቸዋል።

  • ጁላይ 08 2018, 98 ቀን በሥራ ገበታ ላይ
    ፕሬዚደንት ኢሳያስ አፈወርቂ (በስተቀኝ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድን (በስተግራ) ሲቀበሉ

    ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ወደ ኤርትራ መዲና አስመራ አቅንተዋል። ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ አየር ማረፊያ በመገኘት ኤርትራውያን ደግሞ በነቂስ አደባባይ ወጥተው ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል። ጉብኝቱ ባለፉት ሁለት አስርታት የነበረውን ውጥረት ያረገበና በሁለቱ ሀገሮች መካከል ሰላም ስለማንሰራራቱ ምልክት ነው ተብሏል።

  • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ቃለ መሀላ ሲፈጽሙ
    ቃለ መሀላ ፈጸሙ

    ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢህአዴግ ሊቀ መንበር ከሆኑ ከሳምንት በኋላ በሕዝብ እንደራሴዎች ፊት ቃለ መሀላ ፈጸሙ። በእለቱ ስለ ህብረትና ለውጥ ተናግረዋል።

  • ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለሲዳማ የሀገር ሽማግሌዎች ሰላምታ ሲሰጡ
    ለሥልጣን ዘመን ገደብ?

    ሥልጣን ይዘው ብዙም ሳይቆይ በክልል ከተሞች እየተዘዋወሩ ነዋሪዎችን ማነጋገር ያዙ። በደቡብ ክልል ሀዋሳ ከተማ ተገኝተው የጠቅላይ ሚኒስትር የስልጣን ዘመን ከአስር አመት እንደማይዘል አሳውቀዋል።

  • የጅቡቲ ፕሬዚዳንት (በስተግራ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ (በስተቀኝ)
    ወደ ጅቡቲ አቀኑ

    ከሀገር ውጪ መጀመሪያ ያቀኑት ወደ ጅቡቲ ሲሆን ከጅቡቲው አቻቸው ጋር ስለ ኢኮኖሚያዊ ትስስርና የቀጠናው ሰላም ተወያይተዋል። ኢትዮጵያውያን ታራሚዎችንም ከጅቡቲ አስፈትተዋል።

  • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (በስተቀኝ) ከአንዳርጋቸው ጽጌ ጋር ሲጨባበጡ (በስተግራ)
    አንዳርጋቸው ጽጌ ከእስር ተለቀቁ

    እንግሊዛዊ ዜግነት ያላቸው የግንቦት 7 መሪ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የሞት ፍርዳቸው ተሽሮ ከእስር ተለቀቁ። በተለቀቁ ማግስት በብሔራዊ ቤተ መንግስት ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ተገናኙ።

  • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (በስተግራ) ልዑል መሀመድ ቢን ሰልማን አብዱል (በስተቀኝ)
    ከአፍሪካ ውጪ የመጀመርያው ይፋዊ ጉብኝት

    ከአፍሪካ ውጪ ባደረጉት የመጀመሪያ ጉብኝት ወደ ሳውዲ አረቢያ አምርተው ለሁለት ቀናት በሁለትዮሽ ጉዳዮች እንዲሁም በአለም አቀፍ ሁነቶት ከልዑል መሀመድ ቢን ሰልማን አብዱል ጋር ተወያይተዋል። ጉብኝታቸውን ተከትሎ ከ1000 በላይ ኢትዮጵያውያን ታራሚዎች ከእስር ተለቀዋል።

  • የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በውይይት ላይ
    የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተነሳ

    የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለስድስት ወራት የተደነገገውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አነሳ። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ይነሳል ከተባለበት ግዜ ሁለት ወራት ቀድሞ የተነሳው በሀገሪቱ ሰላምና መረጋጋት በመስፈኑ ነው ተብሏል።

  • የኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት በስብሰባ ላይ
    የኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ውሳኔ

    ገዢው ፓርቲ በመንግስት ባለቤትነት ስር የነበሩትን ቴሌ ኮሙኑኬሽንና አየር መንገድን ለሀገር ውስጥ እና ለውጭ ባለሀብቶች በከፊል ለመሸጥ መወሰኑ ዋነኛ የፖሊሲ ለውጥ ነበር። በሥራ አስፈፃሚው መግለጫ መሰረት ይህ ውሳኔ ያስፈለገው የሀገሪቱን ፈጣን እድገት ለማስቀጠል ነው። በዚሁ ዕለት ነበር የአልጀርሱን ስምምነት ሙሉ በሙሉ ለመተግበር የተወሰነው።

  • የቀድሞ የመከላከያ ኢታማዦር ሹም ሳሞራ የኑስ
    የወታደራዊና የደህንነት አመራሮች ስልጣን ሽግሽግ

    ጠቅላይ ሚኒሰትሩ በጀነራል ሳሞራ የኑስ ምትክ ጀነራል ሰአረ መኮንንን የመከላከያ አዛዥ አድርገዋል። የፀጥታና ደህንነት ኃላፊው አቶ ጌታቸው አሰፋም በአቶ አደም መሀመድ ተተክተዋል።

  • ጠቅላይ ሚኒሰትር ዐብይ አህመድ (በስተግራ) ዩዌሪ ሙሴቪኒ (በስተቀኝ)
    ኡጋንዳ -ግብፅ

    ጠቅላይ ሚኒሰትር ዐብይ አህመድ የኡጋንዳን ከፍተኛውን ሜዳሊያ ተሸልመው በሚቀጥለው ቀን ወደ ግብፅ ተጉዘው የግብፅ አቻቸውን ያገኙ ሲሆን ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱም ከግብፅ የተለቀቁ ታራሚዎችን እንዲሁም የኦነግ አመራር አባላትን ይዘው ተመልሰዋል።

  • እጅና እግሩ በአንድነት የታሰረ ሰው ንድፍ
    መንግስት በሽብር ተግባር

    ጠቅላይ ሚኒሰትሩ መንግሥት የፖለቲከኛ እስረኞችን ያሰቃይ እንደነበር ይህም ህገ መንግስታዊ እንዳልሆነ ገልፀዋል። ‘ ማሰርና ማሰቃየት ኢ-ህገመንግስታዊ ነው። ሽብርተኝነት ህገ መንግስቱ ከሚፈቅደው ውጭ ስልጣን ላይ ለመቆየት የሚደረግ እርምጃንም ይጨምራል' ብለዋል።

  • የቀይ መስቀል አባላት የተጎዱትን ሲያክሙ
    የቦንብ ፍንዳታ በድጋፍ ሰልፉ ላይ

    ቅዳሜ ሰኔ 16 በመስቀል አደባባይ ለድጋፍ በወጡ ሰልፈኞች ላይ በደረሰ የቦንብ ፍንዳታ ሁለት ሰዎች ሞተዋል። ከፍንዳታው በኋላ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥቃቱ የእለቱን ስሜት ለማጠልሸት የተቀነባበረ ነው ብለዋል።

  • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ የኤርትራን ልዑካን ሲቀበሉ
    የኤርትራ ልዑካን በኢትዮጵያ

    የኤርትራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን አባላት አዲስ አበባ ሲደርሱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አቀባበል አድርገውላቸዋል። ኢትዮጵያና ኤርትላ ላለፉት 20 ዓመታት አለመግባባት ውስጥ ቆይተዋል። እንደ ኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከሆነ የሁለቱ ሀገራት መሪዎች በቅርቡ ይገናኛሉ።

  • በሽብርተኛነት ተፈርጆ የነበረው ኦነግ ባንዲራ በመስቀል አደባባይ ከፍ ብሎ ሲውለበለብ
    አሸባሪዎች አይደሉም

    የሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት አባላት በሽብርተኝነት ተፈርጀው የነበሩትን ኦነግ፣ ኦብነግ እና ግንቦት 7 ሽብርተኞች አይደሉም በማለት ከሽብርተኛ ድርጅቶች ዝርዝር አውጥቷቸዋል።

  • ፕሬዚደንት ኢሳያስ አፈወርቂ (በስተቀኝ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድን (በስተግራ) ሲቀበሉ
    አስመራ ደረሱ

    ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ወደ ኤርትራ መዲና አስመራ አቅንተዋል። ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ አየር ማረፊያ በመገኘት ኤርትራውያን ደግሞ በነቂስ አደባባይ ወጥተው ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል። ጉብኝቱ ባለፉት ሁለት አስርታት የነበረውን ውጥረት ያረገበና በሁለቱ ሀገሮች መካከል ሰላም ስለማንሰራራቱ ምልክት ነው ተብሏል።

ምስጋና

ገፁን ያበጃጀው፡ ዊሊያም ሙሊ፣ ዲዛይን ያደረገው፡ ሚሊ ዋቺራ መሰናዶ፡ የአፍሪካ ቀንድ አገልግሎት

ምስሎቹ የተወሰዱት

Getty Images, Fitsum Arega Twitter, Fana broadcasting Facebook Page, EBC Facebook Page, Yidnekew Abreha, HRW,Fitsum Arega