በአዲስ አበባ ከተማ ሊታዩ የሚገባቸው 5 ታሪካዊ ቤቶች

የአፈንጉስ አጥናፍ ሰገድ ቤት ካዛንችስ አከባቢ የሚገኘ ሲሆን አሁን የልቤ ፋና ት/ቤት ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል። ይህ ቤት የተገነባው በ1884 ዓ.ም ሲሆን የቤቱ ባለቤት የነበሩት አፈንጉስ አጥናፍ ሰገድ ከፋሽስት ጣሊያን ጦር ጋር በተደርጋው የማይጨው ጦርነት ላይ ተሰውተዋል።

የአፄ ምኒሊክ ቤተመንግስት
የምስሉ መግለጫ, 1. የአፄ ምኒሊክ ቤተ-መንግስት ይህን ጥንታዊ ቤት አፄ ምኒሊክ በ 1875 ዓ.ም ያሰገነቡት ሲሆን በአዲስ አበባ ከተማ ታሪክም የመጀመሪያው ቤተ-መንግስት ነው። ይህን ታሪካዊ ቤት አሁን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቅድስት ማርያም ቤተ-ክርስቲያን ታስተዳድራለች። የጥንታዊ ቤቱ አብዛኘው ክፍል ከድንጋይና ከጭቃ የተገነባ ሲሆን ወራጁ የጥድ እንጨት ነው እንዲሁም ማገሩ የተጠፈረው በበሬ ቆዳ ነው።
የአፄ ምኒሊክ ቤተ-መንግስት
የምስሉ መግለጫ, በግቢው ውስጥ ሶስት ቤቶች ይገኛሉ። የመጀመሪያው የእንግዶች ማረፊያ ሲሆን ሁለተኛው ቤት ደግሞ የንጉሱና የንግስቲቱ መኝታ ቤትና ጌጣጌጥ እንዲሁም የጦር መሳሪያ ማሰቀመጫ ነው። በሶሰተኛው ቤት ውስጥ የመሰብሰቢያ፣ መመገቢያ፣ የማርና የስጋ ማሰቀመጫ ክፍሎች ማየት ይቻላል።
የአፄ ምኒሊክ ቤተመንግስት
የምስሉ መግለጫ, የአከባቢው አሰጎብኚዎች እንደሚሉት ከሆነ አፄ ምኒሊክ ወደ አድዋ የዘመቱት ከዚሁ ቤተ-መንግሰታቸው ተነስተው ሲሆን ከድል መልስም የገቡት ወደዚሁ ቤተ-መንግሰታቸው ነበር። ከዚህም በተጨማሪ በግቢው ውስጥ የሚታየው ባህር-ዛፍ አፄ ሚኒሊክ ከአውሰትራሊያ ካስመጧቸው ባህር-ዛፎች አንዱ እንደሆነ ይናገራሉ።
የራስ ተሰማ ናደው ተሰማ ቤት
የምስሉ መግለጫ, 2. የራስ ተሰማ ናደው ቤት ይህ ጥንታዊ ቤት በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 07 ጥቁር አምበሳ ሆሰፒታል ኖክ ማደያ አከባቢ የሚገኝ ሲሆን አሁን የሜ/ጀ/ ሃየሎም አርአያ የመጀመሪያ ደርጃ ት/ቤት በመሆን እያገለገለ ይገኛል። በጊዜው የቤቱ የመብራት አምፑሎችና ጌጦች ከአውሮፓ መጥተው የተገጠሙና ልዩ ስለነበሩ ቤቱ ሸዋን ገረመው በማለት ይጠራ ነበር። እንዲሁም የዚህን ቤት የመብራት አምፑሎችና ጌጦች አፄ ሃ/ስላሴ በቤተ-መንግስታቸው ዝግጅት ሲኖራቸው ይዋሱት ነበር ይባላል።
የራስ ተሰማ ናደው ተሰማ ቤት
የምስሉ መግለጫ, ምንም እንኳን ከአውሮፓ የመጡት በእርግጥም እንኚህ አምፑሎችና ጌጦች ስለመሆናቸው ማረጋገጫ ባይኖርም በምስሉ ላይ ያለውን አይነት አምፑሎችና ጌጦች አሁንም በቤቱ ውስጥ ተንጠልጥለው ይገኛሉ።
የአፈንጉስ አጥናፍ ሰገድ ቤት
የምስሉ መግለጫ, 3. የአፈንጉስ አጥናፍ ሰገድ ቤት ካዛንችስ አከባቢ የሚገኘ ሲሆን አሁን የልቤ ፋና ት/ቤት ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል። ይህ ቤት የተገነባው በ1884 ዓ.ም ሲሆን የቤቱ ባለቤት የነበሩት አፈንጉስ አጥናፍ ሰገድ ከፋሽስት ጣሊያን ጦር ጋር በተደርጋው የማይጨው ጦርነት ላይ ተሰውተዋል።
የአፈንጉስ አጥናፍ ሰገድ ቤት
የምስሉ መግለጫ, በጊዜው ከነበሩ ቤቶች ጋር ሲነጻጸር ይህ ቤት አብዛኛው ክፍሉ ከኖራ ድንጋይና ከሲሚንቶ የተገነባ ነው። የዚህ ጥንታዊ ህንፃ ምድር ቤት እንደ ኩሽና ሆኖ ያገለግል ነበር። የቤቱ ዲዛይነር መሃመድ ወሌ እንደሆኑ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
የአፈንጉስ አጥናፍ ሰገድ ቤት
የምስሉ መግለጫ, ከዚህም በተጨማሪ ከላይኛው ፎቅ ወደ ምድር ቤት የሚያወርድ ውብ የሆነ የመውረጃ ደረጃዎች በውስጥና በውጪ የቤቱ ክፍል የተሰራለት ቢሆንም ከእድሜና ከአገልግሎት ብዛት እርጅና ተጭኖታል።
የአፈንጉስ ነሲቡ መሰቀሎ ቤት
የምስሉ መግለጫ, 4. የአፈንጉስ ነሲቡ መሰቀሎ ቤት ይህ ቤት በአራዳ ክ/ከተማ ወረዳ 07 ሳንፎርድ ት/ቤት አከባቢ ይገኛል። የተገነባው 1898 ዓ.ም ሲሆን የቤቱ ባለቤት የነበሩት አፈንጉስ ነሲቡ መሰቀሎ በሃገራችን ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ አፄ ምኒሊክ የሚኒስትሮች ምክር ቤትን ሲያቋቋሙ የመጀመሪያው የፍርድ ሚኒስትር በመሆን የተሾሙ ናቸው። በጊዜው አፈንጉስ ነሲቡ የሚሰጡት ፍርድ ከበድ ያለ በመሆኑ ተከሳሾች እሳቸው ፊት መቅረብን አይመርጡም ነበር።
የአፈንጉስ ነሲቡ መሰቀሎ ቤት
የምስሉ መግለጫ, ይህ ጥንታዊ ቤት ባለ አንድ ፎቅ ሲሆን ምድር ቤቱ እንደ ኩሽና ሆኖ ያገለግል ነበር። የታችኛው የቤቱ ክፍል በጠንካራ መሰረት ላይ የተገነባ ቢሆንም ከእድሜ ብዛትና ከአያያዝ ጉድለት እጅጉን ተጎሳቁሏል።
የአፈንጉስ ነሲቡ መሰቀሎ ቤት
የምስሉ መግለጫ, በአሁኑ ወቅት በቤቱ ውስጥ ከ40 በላይ ቤተሰብ ይኖራሉ። በቤቱ ዙሪያ ላይ በርካታ ቅጥልጣይ ቤቶች ተገንብተዋል ከዚህ በተጨማሪም የጥንታዊ ቤቱ በርካታ መስኮቶችና በሮች በላሜራ ብረቶች ተቀይረዋል።
የአፈንጉስ ነሲቡ መሰቀሎ ቤት
የምስሉ መግለጫ, ለዚህ ጥንታዊ ቤት አስፈላጊ የሆነ አስቸኳይ ጥገና ካልተካሄደለት የነዋሪዎቹም ሆነ የቤቱ ህልውና አደጋ ላይ ነው።
የልዑል ራስ ስዩም መንገሻ ቤት
የምስሉ መግለጫ, 5. የልዑል ራስ ስዩም መንገሻ ቤት ከላይ የተዘረዘሩትን ቤቶች ጨምሮ በከተማዋ ማስተር ፕላን ላይ በቅርስነት የተመዘገበው ይህ ቤት ፈረንሳይ ለጋሲዮን አካባቢ የሚገኘው የልዑል ራስ ስዩም መንገሻ ቤት ነው። ይህ ጥንታዊ ግዙፍ ቪላ ቤት ነው። የአሰራሩም ሁኔታ የጊዜውን የቤት አሰራርን ጥበብ የሚያሳይ ነው።
የልዑል ራስ ስዩም መንገሻ ቤት
የምስሉ መግለጫ, ልክ አንደ አፈንጉስ ነሲቡ መሰቀሎ ቤት በዚህም ቤት ውስጥ በርካታ አባወራዎች ይኖራሉ። በአንድ ወቅት የአንድ ሰው መኖሪያ የነበር ቤት አሁን ከ30 በላይ አባወራዎች ይኖሩበታል። በቤቱ ዙሪያም በርካታ ቅጥልጣይ ቤቶች ተገንብቷል።
የልዑል ራስ ስዩም መንገሻ ቤት
የምስሉ መግለጫ, ለዚህም ጥንታዊ ቤት አስቸኳይ ጥገና ካልተካሄደ የቤቱና የነዋሪዎቹ ህልውና አደጋ ላይ ነው።