ሱዳን የኡጋንዳው ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሜሴቪኒ ላይ ቅሬታ አቀረበች

የፎቶው ባለመብት, @KagutaMuseveni
ሱዳን፣ የፈጥኖ ደራሽ ኃይል አዛዡን ተቀብላ ያስተናገደችው ኡጋንዳ ላይ ተቃውሞዋን አሰማች።
የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኡጋንዳ ባለሥልጣናት ከአርኤስኤፍ አዛዥ ሞሐመድ ሃምዳን ዳጋሎ (ሄሜቲ) ራሳቸውን እንዲያርቁ ጠይቀዋል።
የኡጋንዳው ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ የሱዳኑ ፈጥኖ ደራሽ ኃይል አዛዥ በቤተመንግሥታቸው ተቀብለው ያነጋገሩት አርብ የካቲት 13/2018 ዓ.ም. ነበር
የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ በሱዳን በቀጠለው የእርስ በእርስ ጦርነት ውሰጥ በርካታ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ፈጽሟል በሚል ይከሰሳል።
ካርቱም የሁለቱን አገራት ግንኙነት ለመጠበቅ እንደምትፈልግ ገልጻ በውስጥ ጉዳይዋ ግንማንኛውንም የውጭ ጣልቃ ገብነት እንደማትቀበል ተናግራለች።
ከወራት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በአደባባይ የታዩት የአርኤስኤፍ መሪ ሃምዳን ዳጋሎ ጉብኝት ብዙዎችን አስገርሟል።
ሱዳን፣ ኡጋንዳ የግጭቱን አሳሳቢነት ችላ በማለት እና ዓለም አቀፍ ደንቦችን በመጣስ ከአማፅያን አዛዥ ጋር በመገናኘቷ ወቀሳዋን ሰንዝራለች።
ነገርግን በአፍሪካ ኅብረት ሁለቱን ተፋላሚ ወገኖች እንዲያደራድሩ የተሾሙት ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ከሄሜቲ ጋር አርብ የተካሄዱት ስብሰባ የሱዳንን የእርስ በርስ ጦርነት የሚያበቃበትን መንገድ በማፈላለግ ላይ ያተኮረ ነው ብለዋል።
የቀጠናው መንግሥታት በግጭቱ ውስጥ ካሉ ተቀናቃኝ ወገኖች ጋር በመወገን ትችት ሲሰነዘርባቸው ቆይቷል።




















