እንዴት አንድ አንበጣ ወረርሽኝ እንደሚሆን

ከወራት በፊት ግዙፍ የበረሃ አንበጣ መንጋ የአፍሪካ ቀንድንና ደቡብ እስያን እያካለለ ያገኘውን ሰብል በማውደም የአካባቢውን ሕዝብ የምግብ አቅርቦትና ህይወት አደጋ ላይጥሎ ነበር። አሁንም በድጋሚ በድጋሚ እየተራባ ይገኛል። ይህም በ25 ዓመት ውስጥ ያጋጠመ የከፋ የአንበጣ መንጋ ወረርሽኝ ነው። እንዴት እዚህ አስከፊ ደረጃ ላይ ደረሰ?

የበረሃ አንበጣው ዝርዝር ገጽታ

የይህን የሚመስለው የበረሃ አንበጣ ተነጥሎ ብቻውን የሚኖር ነው። ከእንቁላል ተነስቶ በማደግ መብረር የሚችል አንበጣ ይሆናል። ቀላልና ብዙም ያልጎላ አኗኗር አለው።

በረሃ አንበጣው ገላጭ ገጽታ

አንድ አንበጣ በተከታታይ በተለያዩ ደረጃዎች ውስጥ ያልፋል። ቁጥራቸው በሚያንስበትና የሚበሉት ሰብል በሚያጥርበት ጊዜ በብቸኝነት መኖራቸውን በመተው በጋራ ይሆናሉ።

በዚህ ወቅት ቀለማቸውን በመቀየር በቡድን የሚጓዝ አውዳሚ መንጋን ይፈጥራሉ።

እንዲህ ያለው የአንበጣ መንጋ ግዙፍ ሊሆን ይችላል። ቁጥራቸውም እስከ 10 ቢሊየን፤ የሚሸፍኑትም ቦታ በመቶዎች ኪሎ ሜትር ሊሆን ይችላል። የአንበጣ መንጋው በቀን እስከ 200 ኪ.ሜ በመሸፈን ያገኙትን እየበሉ በመራባት የአርሶ አደሮችን ህይወት አደጋ ላይ ይጥላሉ።

ተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የምግብና የእርሻ ድርጅት እንዳለው አማካይ የአንበጣ መንጋ 2500 ሰዎችን ለዓመት የሚመግብ ምርትን ሊያወድም ይችላል።

ከ15 ዓመት በፊት በምዕራብ አፍሪካ ተከስቶ የነበረ የአንበጣ መንጋ 2.5 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ የሰብል ውድመትን ማስከተሉን የተባበሩት መንግሥታት ገልጿል።

ከ60 ዓመታት በፊትም ከባድ የሚባሉ የአንበጣ መንጋ ወረርሽኝ አጋጥሞ ነበር። ክስተቶቹም በርካታ አህጉራትን ያካተቱ ስለነበሩ "ወረርሽኝ" ከሚባሉበት ደረጃ ላይ ደርሰው ነበር።

የመንግሥታቱ ድርጅት እንደሚገምተው የበረሃ አንበጣ ከምድራችን 10 ነዋሪዎች የአንዱን ህይወት ይነካል። ይህም አንበጣን ከቦታ ቦታ የሚንቀሳቀስ አደገኛ ፍጥረት አስብሎታል።

የይህን የሚመስለው የበረሃ አንበጣ ተነጥሎ ብቻውን የሚኖር ነው። ከእንቁላል ተነስቶ በማደግ መብረር የሚችል አንበጣ ይሆናል። ቀላልና ብዙም ያልጎላ አኗኗር አለው።

አንድ አንበጣ በተከታታይ በተለያዩ ደረጃዎች ውስጥ ያልፋል። ቁጥራቸው በሚያንስበትና የሚበሉት ሰብል በሚያጥርበት ጊዜ በብቸኝነት መኖራቸውን በመተው በጋራ ይሆናሉ።

በዚህ ወቅት ቀለማቸውን በመቀየር በቡድን የሚጓዝ አውዳሚ መንጋን ይፈጥራሉ።

እንዲህ ያለው የአንበጣ መንጋ ግዙፍ ሊሆን ይችላል። ቁጥራቸውም እስከ 10 ቢሊየን፤ የሚሸፍኑትም ቦታ በመቶዎች ኪሎ ሜትር ሊሆን ይችላል። የአንበጣ መንጋው በቀን እስከ 200 ኪ.ሜ በመሸፈን ያገኙትን እየበሉ በመራባት የአርሶ አደሮችን ህይወት አደጋ ላይ ይጥላሉ።

ተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የምግብና የእርሻ ድርጅት እንዳለው አማካይ የአንበጣ መንጋ 2500 ሰዎችን ለዓመት የሚመግብ ምርትን ሊያወድም ይችላል።

ከ15 ዓመት በፊት በምዕራብ አፍሪካ ተከስቶ የነበረ የአንበጣ መንጋ 2.5 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ የሰብል ውድመትን ማስከተሉን የተባበሩት መንግሥታት ገልጿል።

ከ60 ዓመታት በፊትም ከባድ የሚባሉ የአንበጣ መንጋ ወረርሽኝ አጋጥሞ ነበር። ክስተቶቹም በርካታ አህጉራትን ያካተቱ ስለነበሩ "ወረርሽኝ" ከሚባሉበት ደረጃ ላይ ደርሰው ነበር።

የመንግሥታቱ ድርጅት እንደሚገምተው የበረሃ አንበጣ ከምድራችን 10 ነዋሪዎች የአንዱን ህይወት ይነካል። ይህም አንበጣን ከቦታ ቦታ የሚንቀሳቀስ አደገኛ ፍጥረት አስብሎታል።

ከ1926-2019 (እአአ) የአንበጣ ወረርሽኝ እንዳጋጠማቸው ሪፖርት ያደረጉ አገራት
ዓመትዝቅተኛ ቁጥርማሻቀብ ወይም መቀነስወረርሽኝ
20190180
2018000
2017000
2016500
2015200
2014700
20131000
2012900
2011700
2010400
2009500
2008800
20071300
2006100
20050200
20040230
2003500
2002000
2001000
2000200
1999400
1998700
19971200
19961500
19951500
19941300
19932000
1992500
1991000
1990300
19890150
19880026
19871500
19861200
1985200
1984000
1983700
1982500
1981500
1980600
1979040
19780150
1977300
1976900
1975700
19741100
1973700
1972500
1971400
1970700
19690110
19680250
1967700
1966200
1965400
1964600
19630100
19620290
19610290
19600044
19590047
19580041
19570037
19560035
19550043
19540040
19530043
19520027
19510410
19500330
1949900
19481200
19470290
19460360
19450042
19440047
19430043
19420035
19410240
1940060
1939500
1938300
1937600
1936600
1935600
1934090
19330180
19320027
19310035
19300045
19290041
19280034
19270220
1926080
ምንጭ፡ FAO
ማስታወሻ፡ 'ዝቅተኛ ቁጥር' ማለት አንበጣዎች የሚሸፍኑት ቦታ ትንሽ ሲሆን፤ 'ማሻቀብ' ደግሞ አንበጣዎቹ እየተራቡ በርካታ ወረርሽኝ እንዲፈጠር ሲያደርጉ ነው። 'ወረርሽኝ' ማለት ደግሞ በከፍተኛ ሁኔታ ሰፊ ቦታን የሚሸፍን የአንበጣ መንጋ ከዓመት በላይ ሲከሰት ነው። ወረርሽኙ ሲያበቃ ደግሞ 'መቀነስ' ይባላል።

አዲስ የአንበጣ መንጋ እየተፈለፈለ ነው።

ከሦስት ወራት በፊት ያጋጠመው የአንበጣ መንጋ በአስር ዓመታት ውስጥ ካጋጠመው የከፋው ሲሆን፤ ጂቡቲን፣ ኢትዮጵያንና ሶማሊያን ጨምሮ የአፍሪካ ቀንድን በማዳረስ ሰብሎችንና የእንስሳ ግጦሽን አውድሟል። ይህም የአካባቢውን አገራት የምግብ ደህንነት አደጋ ላይ ጥሎታል።

የአንበጣ መንጋው በጥርና በየካቲት በፍጥነት ተዛምቶ ኢትዮጵያን፣ ሶማሊያንና ኬንያን በማዳረስ በምሥራቅ አፍረካ ተዛምቷል። ወረርሽኙ ለኢትዮጵያና ለሶማሊያ በ25 ዓመት እንዲሁም ለኬንያ ደግሞ በ70 ዓመት ውስጥ ካጋጠሟቸው የከፋው ነው።

የዓለም ምግብና እርሻ ድርጅት (ፋኦ) ስጋቱን እንደገለጸው ከሆነ ከመጋቢት በኋላ ያለው እርጥብ የአየር ሁኔታ ሁለተኛ ዙር የአንበጣ አንበጣ ወረርሽኝ በማስከተል በአካባቢው ሕዝብ ህይወት ላይ "ታይቶ የማያውቅ ስጋትን" ደቅኗል።

የአንበጣ መንጋውን የመቆጣጠሩ ሥራ በፍጥነት ካልተከናወነ መንጋው በ20 እጅ ሊጨምር እንደሚችል ፋኦ አስጠንቅቋል።

በአንበጣ ስጋት ውስጥ ያሉ አገራት ቁጥር

የአፍሪካ ቀንድ፣ የቀይ ባሕር አካባቢና የሕንድና ፓኪስታን ድንበር አካባቢ ያለውን የአንበጣ ወረራ የሚያሳይ ካርታ። የአንበጣ መንጋው ኢትዮጵያና ኬንያ ውስጥ የተከሰተ ሲሆን ወደ ሌሎች አገራትም ሊሄድ ይችላል።ምንጭ፡ FAO፣ የካቲት 2020

ይህም በግጭቶች፣ በድረቅና በጎርፍ ምክንያት ከፍተኛ የምግብ እጥረት ባለበት በምሥራቅ አፍሪካ ውስጥ ከባድ ጉዳትን ያስከትላል። በተጨማሪም የአንበጣ መንጋው እየተራባ ባለባቸው በኢራንና በየመን ጉዳቱ የባሰ እንደሚሆን ፋኦ ገልጿል።

እስካሁንም በምሥራቅ አፍሪካ አገራት ውስጥ የሚገኙ በአስር ሺህ ሔክታሮች የሚገመት ግጦሽ መሬት በአንበጣ መንጋው ወድሟል።

ከጥቂት ወራት በፊት የአንበጣ መንጋው በ350 ስኩዬር ኪሎ ሜትር ላይ የሚገኝን 1.8 ቶን የሚመዝን አረንጓዴ እጸዋትን በአንድ ቀን ውስጥ ይመገባል።

ድርጅቱ እንደሚያምነው አንድ መንጋ ኬንያ ውስጥ 40 ኪ.ሜ በ60 ኪ.ሜ የሚሆን ስፋት ያለውን ቦታ ያካልላል።

አንበጣ ምን ያህል መመገብ ይችላል?

ያደገ የበረሃ አንበጣ በቀን የክብደቱን ያህል መመገብ ይችላል። ይህም ማለት 2 ኪ.ግ ይጠጋል።አንድ የበረሃ አንበጣ ምን ያህል መመገብ እንደሚችል የሚያሳይ ስዕላዊ መረጃ። ያደገ የበረሃ አንበጣ በቀን የክብደቱን ያህል 2 ኪ.ግ መመገብ ይችላል። አንድ ስኩዬር ኪሎ ሜትርን የወረረ የአንበጣ መንጋ 35 ሺህ ሰዎች የሚመገቡትን ያህል ሰብል ይበላል።ምንጭ፡ FAO

በኢትዮጵያና በኬንያ ያጋጠመው ሁለተኛው ዙር የአንበጣ ወረራ ከመጀመሪያው የበለጠ ሲሆን፤ የከሁሉ የሚያሳስበው ደግሞ የተከሰተበት ወቅት ነው ነው ሲሉ የፋኦ ከፍተኛ የአንበጣ ትንበያ ባለሙያ ኪት ክሬስማን ይናገራሉ።

"አሁን በእነዚህ አገራት ወቅቱ ዝናብ የሚጀምርበትና ተክሎች የሚተከሉበት ጊዜ ነው። የተዘራው የሚበቅልበት ጊዜ ቢሆንም የአንበጣ መንጋ ወረራው ደግሞ ተከስቷል።"

አሁን የተከሰተው የአንበጣ መንጋ እያደገ ነው ከጥቂት ጊዜ በኋላ ደግሞ እንቁላል በመጣል ሌላ ዙር የአንበጣ መንጋ ምርት በሚሰበሰብበት ጊዜ አድጎ ሰብልን ሊያወድም ይችላል፤ ይላሉ ክሪስማን መንጋው ሁለት ጊዜ የሚያደርሰውን ጉዳት በማሰብ።

እርሻው በአንበጣ የወደመበት የአሊ ቢላ ዋቆ ፎቶ

የአንበጣ ወረርሽኙ የተከሰተው አገራቱ እየጨመረ ያለውን የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ለመቆጣጠር በሚጥሩበትና የእንቅስቃሴ ገደቦችን በጣሉበት ጊዜ ነው።

የ68 ዓመት ዕድሜ ያላቸው አሊ ቢላ ዋቆ በሰሜን ምሥራቅ ኬንያ አርሶ አደር ሲሆኑ፤ ከረጅም ጊዜ ድርቅ በኋላ በቅርቡ በጣለው ዝናብ ጥሩ ምርት እንደሚያገኙ ተስፋ አድርገው ነበር።

ነገር ግን የአንበጣው መንጋ የበቆሎና የቦሎቄ ማሳቸውን አውድሞባቸዋል።

"የአንበጣ መንጋው አብዛኛውን ሰብል በልቶ ያወደመው ሲሆን፤ ያልበላው ደግሞ ደርቋል" ይላሉ። "ይህም ከባድ ጉዳት ነው ያደረሰብን። የደረሰውን ሰብል ብናየውም ልንመገበው ግን አልታደልንም።"

በ1960ዎቹ አጋጥሞ የነበረውን የአንበጣ ወረርሽኝ የሚያስታውሱት አሊ ዋቆ፤ በወቅቱ ሰማዩ በአንበጣ ተሸፍኖ ጨልሞ እንደነበረ ይናገራሉ።

"የፀሐይ ብርሐንን ማየት ስለማይቻል ቀኑ ጨልሞ ነበር" ይላሉ።

የአየር ሁኔታ መዛባቱ ደግሞ ያጋጠመውን ችግር አባብሶታል

አሁን ለተከሰተው የአንበጣ መንጋ ምክንያቱ በ2018-2019 ያጋጠመው ከባድ ነፋስና ዝናብ እንደሆነ ይነገራል።

የበረሃ አንበጣ በምዕራብ አፍሪካና በህንድ ውስጥ ባለና 16 ሚሊዮን ስኩዬር ኪ.ሜ በሚሸፍን ደረቅና በረሃማ አካባቢ ውስጥ ይኖራል።

የተባበሩት መንግሥታት እንደሚለው ግን፤ ከሁለት ዓመት በፊት በደቡባዊ የአረብ ልሳነ ምድር ላይ የነበረው እርጥብና አመቺ የአየር ሁኔታ የአንበጣው ሦስት ትውልድ ሳይታወቅ እንዲራባ እድል ፈጥሮለታል።

የአንበጣው ወረርሽን ማሻቀብ የጀመረው ከአንድ ዓመት በ2018 ነበረ

የአንበጣው መንጋ በተለያዩ ወቅቶች እንዴት እንደሚያድግና ከአረብ ልሳነ ምድር ወደ የአፍሪካ ቀንድ እንዲሁም ወደ ህንድና ፓኪስታን ድንበር እንዴት እንደተዛመተ የሚያሳይ ካርታ።ምንጭ፡ FAO ጥር 2020

ባለፈው ዓመት መግቢያ ላይ የመጀመሪያው መንጋ ወደ የመን፣ ሳኡዲ አረቢያና ኢራን የሄደ ሲሆን፤ እዚያም የበለጠ ተራብቶ ወደ ምሥራቅ አፍሪካ ተዛምቷል።

ተጨማሪ የአንበጣ መንጋ የተፈጠረ ሲሆን በባለፈው የፈረንጆች ዓመት ማብቂያ ላይ በኤርትራ፣ በጂቡቲና በኬንያ ውስጥም ተከስቷል።

ኬንያ ውስጥ ሳምቡሩ በተባለ አካባቢ ያጋጠመ የአንበጣ መንጋ ምስል

የአንበጣ መንጋው በዚህ ወቅት መራባት በቀጣዮቹ ወራት በምሥራቅ አፍሪካ፣ በየመንና በደቡባዊ ኢራን ውስጥ የበለጠ የአንበጣ ወረራን ይፈጥራል ተብሎ ተሰግቷል።

ምንም እንኳን የአንበጣው መንጋ የተከሰተበት መልክአ ምድራዊ አቀማመጥ ካለው ስፋት የተነሳ ለመከላከል አስቸጋሪ ቢሆንም፤ ክሪስማን እንደሚሉት ግን መንጋው ከመስፋፋቱ በፊት በመጀመሪያው ደረጃ ላይ እያለ የተሻለ የመከላከል ሥራ መስራት ይቻል ነበር።

"ወሳኝ በሆኑት አገራት ውስጥ የአንበጣውን መስፋፋት ለመቆጣጠር ከፍ ያለ ውጤታማ ጥረት ተደርጎ ቢሆን ኖሮ አሁን የሚደርሰውን ጉዳት ይቀንሰው ነበር" ይላሉ።

ግዙፉን የአንበጣ መንጋ ለመከላከል ጥረት ሲደረግ

የአንበጣ መንጋው ካለው ብዛትና ሊያደርስ ከሚችለው ውድመት አንጻር በአፍሪካ ቀንድ አጋጥሞ የማያውቅ በመሆኑ የአካባቢው አገራት ለመከላከል ጥረት እያደረጉ ነው።

የአንበጣ መንጋ ወረርሽኙን የመቆጣጠሩ ሥራ በሁለት ወሳኝ ተግባራት ላይ የተመሰረተ ነው፤ እነሱም ክትትል ማድረግና ውጤታማ የቁጥጥር ሥራ ማከናወን ናቸው።

በአንበጣ መንጋን ዙሪያ ትንበያ፣ የቅድሚያ ማስጠንቀቂያና የጊዜ ጥቆማን እንዲሁም የመንጋውን መጠን፣ የሚከሰትበትን ቦታና መራባትን በተመለከተ የዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት የሚያቀርበው ‘የበረሃ አንበጣ መረጃ አገልግሎት' ጥቆማን ይሰጣል።

ነገር ግን አሁን አፍሪካ ቀንድ ውስጥ እንዳጋጠመው አይነት የአንበጣ መንጋው ብዛት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ከደረሰ ቁጥሩን ለመቀነስና ተጨማሪ መንጋዎች እንዳይፈጠሩና እንዳይዛመቱ አስቸኳይ የመከላከል እርምጃ መወሰድ አለበት።

የአንበጣ መንጋን እንዴት መከላከል ይቻላል?

.ምንጭ FAO

ምንም እንኳን አካባቢን የማይጎደዳና ተፈጥሯዊ አንበጣን የማጥፊያ ዘዴ ለመፈለግ ጥናቶች እየተደረጉ ቢሆንም፤ በአሁኑ ወቅት በስፋት ጥቅም ላይ እየዋለ ያለው የመቆጣጠሪያ ዘዴ የሚረጭ ጸረ ተባይ ነው።

በእጅ በሚያዝ መርጫ፣ በመኪና ወይም በአውሮፕላን ሁሉንም የአንበጣ መንጋ ኢላማ በማድረግ የሚረጨው ጸረ ተባይ ኬሚካል በአንጻራዊ አጭር ጊዜ ውስጥ ነፍሳቱን ይገድላል።

በዚህም ምክንያት ፋኦ በአሁኑ ወቅት ከመንግሥታት ጋር በመተባበር ጸረ አንበጣ መድኃኒት በአውሮፕላን አማካይነት እየረጨ ይገኛል።

"አሁን ያለው አንበጣ እድገቱን የጨረሰ መንጋ በመሆኑ በአውሮፕላን ለሚደረግ የመከላከል ዘመቻ አመቺ ነው። በዚህም የሚያድጉትንና እንቁላል የሚጥሉትን ቁጥር ለመቀነስ ይቻላል።"

ይህ አንበጣውን የመቆጣጠር ሥራ ከወራት በፊት ከነበረው በተሻለ ውጤታማ ነው ይላሉ ክሪስማን፤ በኮሮናቫይረስ ምክንያት የተጣለው የእንቅስቃሴ እገዳ በሥራው ላይ ምንም አይነት እንቅፋትን አለመፍጠሩንም አመልክተዋል።

በአንበጣ የወደመው አርሶ አደሩ አሊ ቢላ ዋቆ ሰብል ምስል

መሰረተ ልማትና ቀደም ያለ ልምድ ስለማይኖራቸው፤ በተለይ ለበርካታ ዓመታት የአንበጣ መንጋ አጋጥሟቸው ለማያውቁ አገራትና አካባቢዎች ክስተቱ እጅግ አስቸጋሪ ፈተናን ደቅኖባቸዋል።

አሁን በአንበጣ መንጋው ላይ የሚወሰደው እርምጃ ቀጥሎ ምን ሊከሰት እንደሚችል የሚወስን ነው። አሁን የተከሰተው የአንበጣ መንጋ ተጨማሪ ድንበሮችን በማቋረጥ ሰፊ አካባቢን ካጠቃና በርካታ ሰብልን የሚያወድም ከሆነ፤ "ወረርሽኝ" እንደተከሰተ ሊታወጅ ይችላል።

በዚህም ምክንያት "ሁሉም በመተባበር ዕወቀትና ክህሎትን በመጋራት፤ የአንበጣ መንጋው የበለጠ ጉዳት እንዳያደርስ መከላከል ከተቻለ የከፋ አደጋን መስቀረት ይቻላል" ሲሉ ክሪስማን መክረዋል።

ነገር ግን የትኛውም እርምጃ ለኬንያዊው አርሶ አደር አሊ ቢላ ዋቆና ለቤተሰቡ የዘገየ ነው። እነሱም የአንበጣውን መንጋ ለመከላከል ማድረግ የሚችሉት ነገር ሰብል ላይ ለማረፍ ዝቅ ሲል ጄሪካኖችን በመደብደብና በመጮህ ማባረር ብቻ ነው።

ቢሆንም አርሶ አደር አሊ ቢላ ዋቆ ስለተከሰተው የአንበጣ መንጋ የእራሳቸው ምላሽ አላቸው።

"የሆነው የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው። ይህም የእርሱ ሠራዊት ነው" ይላሉ።

የተሳተፉ

ጽሁፍና ዝግጅት በሉሲ ሮጀርስ፣ የመስክ ዝግጅት በጆይ ኢንዉድ፣ ዲዛይን በዞኢ ባርቶሎሚው እና ሚሊ ዋቺራ፣ ዝግጅት በቤኪ ረሽ፣ በካትሪዮና ሞሪስ እና ፒዩሪቲ ቢሪር። የአንብጣ ምስሎች በስዊድበርት አር ኦት እና ስቴፈን ሮጀርስ እና ጌቲ ኢሜጅስ። የኬንያ እርሻ ቦታ ምስሎች በቢቢሲ።


በዚህ ጉዳይ ላይ ተጨማሪ