ይህ ዝቅተኛ ዳታን በመጠቀም ጽሑፍ ብቻ የሚቀርብበት የቢቢሲ አማርኛ ድረ ገጽ ነው
በጆ ባይደን የውጪ ጉዳይ ፖሊሲ ውስጥ ምን ታቅዷል?
በዶናልድ ትራምፕ ዘመን የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ግንኙነት ጠላቶቿንም ወዳጆቿንም የቀላቀለ ነበር። ከሩሲያ ጋር ዶናልድ ትራምፕ የተሻሉ ወዳጅ ነበሩ። ነገር ግን ጆ ባይደን ከእርሳቸው በተለየ መልኩ በፑቲን ላይ መራር ይሆናሉ ወይ? የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ነው። የአፍጋኒስታን፣ ቻይና፣ ሰሜን ኮሪያ እና የኢራን ጉዳዮች ዋነኞቹ ናቸው። የአሜሪካን ተጽዕኖ ፈጣሪነት ለመመለስ እና ወዳጅነትን ለመገንባት ብዙ ሥራ ይጠብቃቸዋል። ነገር ግን ከየት ይጀምራሉ?