የሲዳማ ሕዝበ ውሳኔ፡ የሐዋሳ ነዋሪዎች ምን ይላሉ
የሲዳማ ዞን በደቡብ ክልል ውስጥ እንዲቆይ አሊያ ደግሞ እራሱን ችሎ ክልል እንዲሆን የሚወሰንበት ሕዝብ ድምጽ ነገ ይሰጣል። ዞኑ ክልል እንዲሆን መራጮች ድምጽ እንዲሰጡ ሰፊ ቅስቀሳ እየተደረገ ሲሆን፤ በደቡብ ክልል ውስጥ እንዲቆይ ለማድረግ ግን የሚሰጥ መረጃም ሆነ የሚደረግ ቅስቀሳ እንደሌለ ቢቢሲ ያናገራቸው አንዳንድ የሐዋሳ ነዋሪዎች ገልጸዋል።