‘‘ሁሉም አሸባሪዎች ተገድለዋል፤ ኦፕሬሽኑም ተጠናቋል’’

በኬንያዋ መዲና ናይሮቢ ከሚገኙት ቅንጡ ሆቴሎች አንዱ በሆነው ዱሲት2ናይሮቢ የሽብር ጥቃት ተፈጸመ። ለተፈጸመው የሽብር ጥቃት አልሸባብ ኃላፊነቱን እወስዳለሁ ብሏል። እስካሁን ፖሊስ የሸብር ጥቃቱን አልተቆጣጠረም። የተጎጂዎች ቁጥርም ይፋ አልሆነም።

የቀጥታ ሽፋን

  1. የቀጥታ ዘገባችን ተጠናቋል።

    በናይሮቢ ሆቴል ስለተፈጸመው የሽብር ጥቃት በቀጥታ ዘገባችን አዳዲስ መረጃዎች ስናደርሳችሁ ቆይተናል። የኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ''ሁሉም አሸባሪዎች ተገድለዋል፤ ኦፕሬሽኑም ተጠናቋል'' ሲሉ ተናግረዋል። እኛም የቀጥታ ዘገባችንን ጨርሰናል። ከዚህ ሁነት ጋር በተያያዘ ሌሎች የሚወጡ አዳዲስ መረጃዎችን በድረ-ገጻችን እናቀብላችኋለን።

    ለነበረን ቆይታ እናመስግናለን።

  2. "50 ሰዎች የደረሱበት አልታወቀም"

    የ X ይዘትን ይለፉት
    ይዘቱን X ይፈቅዳሉ?

    ይህ ጽሑፍ በX. የቀረበ ይዘት ይዟል። ገጹ ቴክኖሎጂዎች ወይም ኩኪዎች ሊኖረው ስለሚችል ገጹ ከመከፈቱ በፊት የእርስዎን ፍቃድ እንጠይቃለን። ፍቃድዎን ከመስጠትዎ በፊት የX ኩኪ ፖሊሲ እና የ ማንበብ ይፈልጉ ይሆናል። ይዘቱን ለማንበብ ‘እቀበላለሁ ቀጥል’ የሚለውን ይምረጡ።

    ማሳሰቢያ: በሌሎች ገጾች ላይ ላሉ ይዘቶች ቢቢሲ ኃላፊነት አይወስድም።

    የ X ይዘት መጨረሻ

    የሆቴሉን ጥቃት ተከትሎ አምሳ ግለሰቦች የደረሱበት እንዳልታወቀ የኬንያ ቀይ መስቀል አስታውቋል።

    እስካሁን ድረስ የሞቱ ግለሰቦች አስራ አራት መሆናቸው የተገለፀ ሲሆን፤ ጥቃቱንም ያደረሱት አምስት ግለቦች እንደተገደሉ የኬንያ ፖሊስ አስታውቋል።

    የኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በበኩላቸው 700 ግለሰቦችን ከጥቃቱ መታደግ እንደተቻለ ገልፀዋል።

    አሁንም ሀገሪቷ ከውጭ ሃገራት ለሚመጡ ጎብኝዎች ደህንነቷ የተጠበቀ እንደሆነና ጥቃቱን ያቀነነባበሩ ግለሰቦችንም ወደ ፍርድ እንደሚመጡም ገልፀዋል።

    የኬንያ ቀይ መስቀል የሰጠው ከታች ያለውን መግለጫ ሰጥቷል፡

  3. በጥቃቱ የተጠረጠሩ ሁለት ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር ዋሉ

    የ X ይዘትን ይለፉት
    ይዘቱን X ይፈቅዳሉ?

    ይህ ጽሑፍ በX. የቀረበ ይዘት ይዟል። ገጹ ቴክኖሎጂዎች ወይም ኩኪዎች ሊኖረው ስለሚችል ገጹ ከመከፈቱ በፊት የእርስዎን ፍቃድ እንጠይቃለን። ፍቃድዎን ከመስጠትዎ በፊት የX ኩኪ ፖሊሲ እና የ ማንበብ ይፈልጉ ይሆናል። ይዘቱን ለማንበብ ‘እቀበላለሁ ቀጥል’ የሚለውን ይምረጡ።

    ማሳሰቢያ: በሌሎች ገጾች ላይ ላሉ ይዘቶች ቢቢሲ ኃላፊነት አይወስድም።

    የ X ይዘት መጨረሻ

    በትናንትናው ዕለት በዱሲት2ናይሮቢ ሆቴል ላይ በደረሰው የሽብር ጥቃት ጋር ተያያዥነት አላቸው ተብለው የተጠረጠሩ ሁለት ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የኬንያው ደይሊ ኔሽን የወንጀልምርመራዎችዳይሬክተር የሆኑትን ጆርጅ ኪኖቲን ጠቅሶ ዘግቧል።

    ኬሙንቶ የተባለችው አንዷ ተጠርጣሪ፤ ኪያምቡ በሚባለው ከናይሮቢ ወጣ ብሎ ባለው አካባቢ ከአሸባሪዎቹ አንዱ ይኖርበት ነበር በተባለበት ቤት ውስጥ ታስራለች በማለት ሲቲዝን የተባለው የኬንያ ቴሌቪዥን ጣብያ ገልጿል።

    ሁለተኛው ተጠርጣሪ ደግሞ ኢስሊ በሚባል በናይሮቢ ውስጥ ባለ ሰፈር በቁጥጥር ሥር መዋሉ ተገልጿል።

  4. በሞት ያልተለያዩት ጓደኛማቾች

    የጋራ ቀብር ሥነ-ሥርዓት

    የ33 ዓመቱ አብደላ ዳሂርና የ31 አመቱ ፌይዛል አሕመድ አዳም ስሚዝ ኢንተርናሽናል ( ኤሲአይ) ድርጅት በልማት አማካሪነት የሚሰሩ ሲሆን የሽብር ጥቃቱ በደረሰበት ወቅትም በዱሲት2ናይሮቢ ሆቴል ውስጥ ባለው ሴክሬት ጋርደን ምግብ ቤት ምሳ እየተመገቡ እንደነበር ሮይተርስ ዘግቧል።

    የሁለቱም ጓደኞችና የቤተሰብ አባላት አቶ አብደላና አቶ ፌይዛልን የማለያዩ ጓደኛሞች ነበሩ በማለት ይገልጿቸዋል ገልጸዋል።

    የአቶ ፌይዛል የሚስት ወንድም አቶ አብዱላሂ ኬይናን "በጣም ከመዋደዳቸውና ከቅርበታቸው የተነሳ ብዙ ሰዎች አብረው ነው የሚሞቱት የሚሉ አስተያየት ይሰጡ እንደነበር” ለሮይተርስ ገልጿል።

    ይሰሩበት የነበረው ድርጅት ድረገፅ እንደሚያሳየው በሶማሊያ ሰላምና መረጋጋትን እንዲሁም ብልፅግናን ለማምጣት በሚሠራው የኤሲአይ ክፍል ይሰሩ ነበር።

    "ብዙዎች የሚወዱት፣ ግርማ ሞገስ የተሞላና አስቂኝ እንደነበር" መሀመድ አብደላጢፍ የተባሉ የአቶ ፌይዛል ጓደኛ ለሮይተርስ ተናግረዋል።

    የአቶ ፌይዛል ባለቤት የሰባት ወር ነፍሰ ጡር እንደነበረችም ተገልጿል።

    የአቶ አብደላ የሊንክዲን ገጽ እንደሚያሳየው ፎቶግራፍ ማንሳት እንደሚወድ፣ በሚያነሳቸው ፎቶዎችም ጥቃት ለደረሰባቸውና በጦርነት ለተጎሳቆሉ ድምፃቸው እንዲሰማና ስለ ጦርነት አስከፊ ጎኖች ዓለምን ለማስተማር” ማጋራት እንደሚወድ ገልጿል።

    በዛሬው ዕለት ለጓደኛሞቹ የጋራ ቀብር ሥነ-ሥርዓት ተደርጎላቸዋል።

  5. ‘ጥቃቱን ያደረሱት አምስቱ ተኳሾች ’

    የኬንያ ፖሊስ ኃላፊው ጆዜፍ ቧኔ የትናንትናውን የሽብር ጥቃት ያደረሱት አምስት ተኳሾች ነበሩ በማለት ለአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ አሳውቋል።

    የጥበቃ ካሜራዎች እንደሚያሳየው ቢያንስ አራት ተኳሾች ከባድ መሣሪያዎችን ታጥቀው ወደ ሆቴሉ ቅጥር ግቢ ሲገቡና ተኩስ ሲከፍቱ ነው።

    የ X ይዘትን ይለፉት
    ይዘቱን X ይፈቅዳሉ?

    ይህ ጽሑፍ በX. የቀረበ ይዘት ይዟል። ገጹ ቴክኖሎጂዎች ወይም ኩኪዎች ሊኖረው ስለሚችል ገጹ ከመከፈቱ በፊት የእርስዎን ፍቃድ እንጠይቃለን። ፍቃድዎን ከመስጠትዎ በፊት የX ኩኪ ፖሊሲ እና የ ማንበብ ይፈልጉ ይሆናል። ይዘቱን ለማንበብ ‘እቀበላለሁ ቀጥል’ የሚለውን ይምረጡ።

    ማሳሰቢያ: በሌሎች ገጾች ላይ ላሉ ይዘቶች ቢቢሲ ኃላፊነት አይወስድም።

    የ X ይዘት መጨረሻ

  6. የኬንያ ሙስሊም አመራሮች የሽብር ጥቃቱን "አረመኔያዊ" ሲሉ አወገዙ

    የ X ይዘትን ይለፉት
    ይዘቱን X ይፈቅዳሉ?

    ይህ ጽሑፍ በX. የቀረበ ይዘት ይዟል። ገጹ ቴክኖሎጂዎች ወይም ኩኪዎች ሊኖረው ስለሚችል ገጹ ከመከፈቱ በፊት የእርስዎን ፍቃድ እንጠይቃለን። ፍቃድዎን ከመስጠትዎ በፊት የX ኩኪ ፖሊሲ እና የ ማንበብ ይፈልጉ ይሆናል። ይዘቱን ለማንበብ ‘እቀበላለሁ ቀጥል’ የሚለውን ይምረጡ።

    ማሳሰቢያ: በሌሎች ገጾች ላይ ላሉ ይዘቶች ቢቢሲ ኃላፊነት አይወስድም።

    የ X ይዘት መጨረሻ

    ከአስር የተለያዩ የእስልምና ድርጅቶች የተውጣጡ መሪዎች በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ትናንት ዱሲት2ናይሮቢ የተፈጸመውን የሽብር ጥቃት አውግዘዋል።

    አልሸባብ ኃላፊነቱን የወሰደው ይህንን ጥቃትም ጠንከር ባለ ቃል በመግለጫቸው አውግዘውታል።

    "አረመኔያዊ ተግባርም" ነው ሲሉ ገልፀውታል።

    ድርጅቶቹም በጋራ የምክርና የደም ልገሳ ቦታዎችን ጥቃቱ በደረሰበት አካባቢ አዘጋጅተዋል።

    ይህ ጋዜጣዊ መግለጫ የተካሄደው በጁሚያ መስጊድ ሲሆን፤ መስጊዱም በቅርቡ የተለያዩ ማስፈራሪያዎች በኢንተርኔት ሲደርስበት መቆየቱ ተገልጿል።

    በአብዛኛው በሶማሊያውያን የሚዘወተረውንም ይህንን መስጊድ ጥቃት እንዲደርስበትም ጥሪ ያደረጉም አሉ።

  7. የሽብር ጥቃት በደረሰበት ሆቴል ሌሎችን ከአደጋ ለማውጣት የሰሩት ግለሰብ እየተሞገሱ ነው

    ያለ ምንም ፍርሃት ግለሰቦችን ከአደጋ ለማውጣት የሰሩት ግለሰብ በኬንያ ማህበራዊ ድረ-ገፅ ተጠቃሚዎች ዘንድ እየተሞገሱ ነው
    የምስሉ መግለጫ, ያለ ምንም ፍርሃት ግለሰቦችን ከአደጋ ለማውጣት የሰሩት ግለሰብ በኬንያ ማህበራዊ ድረ-ገፅ ተጠቃሚዎች ዘንድ እየተሞገሱ ነው

    ኬንያውያን በማህበራዊ ድረገፆቻቸው ይህንን ጥቃት እንወጣዋለን (#WeShallOvercome) እና ኬንያ አትበገርም #KenyaUnbowed በሚሉ የመሰላል (ሀሽታግ) ምልክቶች እያጋሩ ይገኛሉ።

    እነዚህ ሁለት ሃሽታጎች ባለፉት 24 ሰዓታት ብቻ ከ30 ሺህ ጊዜ በላይ በትዊተር ላይ ተጋርተዋል።

    ምስጋና ከተቸራቸው መካከል ኢናያት ካሳም የተሰኙ የአደጋ ጊዜ አሠልጣኝ አንዳቸው ሲሆኑ የሽብር ጥቃቱ ከደረሰበት ሆቴል ብዙ ሰዎች አደጋ እንዳያገኛቸው በማድረግ እንዲያመልጡ ረድተዋል።

    በጎርጎሳውያኑ አቆጣጠር 2013 ዌሰትጌት በተሰኘው የገበያ ማዕከል ደርሶ በነበረው የሽብር ጥቃት ይህ ግለሰብ ሰዎችን ለማትረፍ የተደረገውን ርብርብ በዋነኝነት አስተባብረዋል።

    የኬንያ ታዋቂ ጋዜጠኛ ጄፍ ኮይናንጌ ይህንን ግለሰብ ‘እውነተኛ ጀግና’ ነው በማለት በትዊተር ገፁ ላይ ያሞገሳቸው ሲሆን ይህም መልዕክት ከ11ሺህ ጊዜ በላይ በተከታዮቹ ተወዶለታል።

  8. የዓይን እማኞች ምን አሉ?

    ‘ከጠረጴዛ ስር ተደብቄ ነበር"

    ኤል ጂ ኤሌክትሮኒክስ ተብሎ በሚጠራ ድርጅት የማርኬቲንግ ኃላፊ የሆነው ሂራም ማሻሪያ የመጀመሪያውን ፍንዳታ እንደሰማ ለማምለጥ ሙከራ አድርጎ እንደነበር ለሬውተርስ የዜና አገልግሎት ተናግሯል።

    “የእሳት ማጥፊያውን ይዤ ወደታች ልንወርድ ስንል፤ ከአሸባሪዎቹ መካከል ሁለቱ ወደ አሳንሰሩ ሲተኩሱ ስናይ ተመልሰን ከጠረጴዛችን ስር ተደበቅን” ብሏል።

    አክሎም "ደረጃውንም እየወጡ የአሳንሰሩ በሮችና ወደ ደረጃዎቹ የሚወስዱት በሮች ላይ ሁለት ጊዜ ተከሱዋል።። ከተኳሹ አንዱ የቢሮያችን በር ላይ አንድ ጊዜ ተኩሶ ብቅ ብሎ ትቶን ሄደ”

    ማሻሪያ እንደገለፀው በቢሮው ተደብቆ የቀረ ሲሆን ወደ ጣሪያው የሮጠው የሥራ ባልደረባው ግን ተገድሏል።

    ‘ከመውጣታችን በፊት የስልክ መልዕክት ደርሶን ነበር’

    ከፓሪስ ለስራ የመጣው ማማዱ ዲያ በሽብር ጥቃቱ መሃል እራሱን አገኘው።

    በሆቴሉ አርፈው ከነበሩ ካናዳዊና ቻይናዊ እንግዶችና ከሆቴል አስተናጋጅ ጋር በአንድ ክፍል ውስጥ ተደብቀው ነበር።

    "ፖሊሶች የተደበቅንበትን ክፍል እንደሚያውቁና ከአንድ ሰዓት ተኩል በኋላ መጥተው እንደሚያድኑን አጭር የስልክ መልእክት ደርሶን ነበር" ብሏል።

    ፖሊሶቹ መጥተው ሲያስወጧቸውም ተኳሾቹ እንደሰለጠኑ አልሞ ተኳሾች ሲተኩሱ እንደነበር ተናግሯል።

  9. ለሁለተኛ ጊዜ ከሽብር ጥቃት ያመለጠችዋ

    የ X ይዘትን ይለፉት
    ይዘቱን X ይፈቅዳሉ?

    ይህ ጽሑፍ በX. የቀረበ ይዘት ይዟል። ገጹ ቴክኖሎጂዎች ወይም ኩኪዎች ሊኖረው ስለሚችል ገጹ ከመከፈቱ በፊት የእርስዎን ፍቃድ እንጠይቃለን። ፍቃድዎን ከመስጠትዎ በፊት የX ኩኪ ፖሊሲ እና የ ማንበብ ይፈልጉ ይሆናል። ይዘቱን ለማንበብ ‘እቀበላለሁ ቀጥል’ የሚለውን ይምረጡ።

    ማሳሰቢያ: በሌሎች ገጾች ላይ ላሉ ይዘቶች ቢቢሲ ኃላፊነት አይወስድም።

    የ X ይዘት መጨረሻ

    ከትናንቱ የሽብር ጥቃት በህይወት የተረፈችው ሴት፤ ከስድስት ዓመት በፊት አል ሸባብ ዌስትጌት ተብሎ በሚጠራው የገበያ ማዕከል ላይ ከሰነዘረው ጥቃት ማምለጧን ለኬንያ መገናኛ ብዙሃን ተናገረች። በጎርጎሳውያኑ አቆጣጠር 2013 በደረሰው የሽብር ጥቃት ከ67 ሰዎች በላይ ተገድለዋል።

    ትሬሲ ዋንጂሩ በሆቴሉ ህንጻ ላይ የሚገኝ የውበት ሳሎን አስተዳዳሪ ስትሆን፤ የፍንዳታ ድምጽ እንደሰማች "ምን እየተፈጠረ እንደሆነ ለመረዳት ወደ መስኮት ተራመድኩ" ትላለች። ‘‘ጥቃት እየተሰነዘረብን እንደሆነ ስረዳ ለባልደረቦቼ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ በማሳሰብ ተደበቅን’’ ስትልም ሁኔታውን ገልጻለች።

    ትሬሲ የድረሱልን መልዕክት በፌስቡክ ገጿ ላይ አስፍራ ነበረ። አመሻሽ ላይ ፖሊስ ህይወቷን ታድጓል።

  10. በጥቃቱ ወዳጅ ዘመዶቻቸውን ያጡ ሰዎች ወደ አስከሬን ማቆያ ስፍራ እየተመሙ ነው

    በጥቃቱ ወዳጅ ዘመድ እንደተገደለባቸው የተረዱ ሰዎች ሃዘናቸውን በምሬት ሲገልጹ
    የምስሉ መግለጫ, በጥቃቱ ወዳጅ ዘመድ እንደተገደለባቸው የተረዱ ሰዎች ሃዘናቸውን በምሬት ሲገልጹ

    የኬንያ ቀይ መስቀል ማኅበር ቢያንስ 21 ሰዎች መገደላቸውን ያስታወቀ ሲሆን፤ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ደግሞ በጥቃቱ 14 መሆናቸውን አስታውቀዋል።

    ቺሮሞ ተብሎ በሚጠራው የቀብር ማስፈጸሚያ እና የአስከሬን ማቆያ ስፍራ በርካቶች ተሰባስበው ይገኛሉ።

    በጥቃቱ ወዳጅ ዘመድ እንደተገደለባቸው የተረዱ ሰዎች ሃዘናቸውን በምሬት እየገለጹ ይገኛሉ።

    አል ሸባብ ለጥቃቱ ኃላፊነቱን እወስዳለሁ ማለቱ ይታወሳል።

  11. በትዊተር ገጹ ላይ የተስፋ መቁረጥ መልዕክት ሲያስተላልፍ የነበረው ህይወቱ ተረፈች, በመጸዳጃ ቤት ውስጥ ተደብቆ በትዊተር ገጹ ላይ የተስፋ መቁረጥ መልዕክት ሲያስተላልፍ የነበረው ኬንያዊ ህይወቱ ተረፈች

    ሮናልድ እን'ጌኖ ትናንት ከሰዓት ትዊተር ገጹ ላይ በሆቴሉ መታጠቢያ ቤት ውስጥ መደበቁን እና ጥቃት እየተፈፀመባቸው እንደሆነ ገልጾ ነበር። ከከባድ ፍንዳታ በተጨማሪ ተኩስ መሰማቱንም የተናገረው ሮናልድ "ዛሬ ከሞትኩኝ ፈጣሪዬን እና ቤተሰቤን እንደምወዳቸው ንገሩልኝ" ብሎ የቤተሰብ አባላት ስም ዘርዝሮ ነበር።

    የ X ይዘትን ይለፉት, 1
    ይዘቱን X ይፈቅዳሉ?

    ይህ ጽሑፍ በX. የቀረበ ይዘት ይዟል። ገጹ ቴክኖሎጂዎች ወይም ኩኪዎች ሊኖረው ስለሚችል ገጹ ከመከፈቱ በፊት የእርስዎን ፍቃድ እንጠይቃለን። ፍቃድዎን ከመስጠትዎ በፊት የX ኩኪ ፖሊሲ እና የ ማንበብ ይፈልጉ ይሆናል። ይዘቱን ለማንበብ ‘እቀበላለሁ ቀጥል’ የሚለውን ይምረጡ።

    ማሳሰቢያ: በሌሎች ገጾች ላይ ላሉ ይዘቶች ቢቢሲ ኃላፊነት አይወስድም።

    የ X ይዘት መጨረሻ, 1

    ሮናልድ ትናንት ምሽት 1 ሰዓት አካባቢ የስልኩ ባትሪ እያለቀ መሆኑን በመጥቀስ ሰዎች በጸሎት እንዲያስቡት ጠይቆ ነበር። ከዚያም ለሰዓታት ዕጣ ፈንታው ሳይታወቅ ቆይቶ ነበር።

    ንጋት ላይ ሮናልድ የጸጥታ አስከባሪዎች ህይወቱን እንደታደጉት በትዊተር ገጹ ላይ አስታውቋል።

    የሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ሮናልድ ዛሬ ጠዋት ከቤተሰብ አባላቱ ጋር የተነሳውን ፎቶ ይዘው ወጥተዋል።

    የ X ይዘትን ይለፉት, 2
    ይዘቱን X ይፈቅዳሉ?

    ይህ ጽሑፍ በX. የቀረበ ይዘት ይዟል። ገጹ ቴክኖሎጂዎች ወይም ኩኪዎች ሊኖረው ስለሚችል ገጹ ከመከፈቱ በፊት የእርስዎን ፍቃድ እንጠይቃለን። ፍቃድዎን ከመስጠትዎ በፊት የX ኩኪ ፖሊሲ እና የ ማንበብ ይፈልጉ ይሆናል። ይዘቱን ለማንበብ ‘እቀበላለሁ ቀጥል’ የሚለውን ይምረጡ።

    ማሳሰቢያ: በሌሎች ገጾች ላይ ላሉ ይዘቶች ቢቢሲ ኃላፊነት አይወስድም።

    የ X ይዘት መጨረሻ, 2

  12. "ቢያንስ 24 ሰዎች ተገድለዋል", ቀይ መስቀል "ቢያንስ 24 ሰዎች ተገድለዋል"

    የኬንያ ቀይ መስቀል ማኅበር በዱሲት2ናይሮቢ በደረሰው የሽብር ጥቃት ቢያንስ 24 ሰዎች ተገድለዋል አለ።

    ከደቂቃዎች በፊት ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ለኬንያ ሕዝብ ባስተላለፉት መልዕክት የ14 ሰዎች ህይወት አልፏል ብለው ነበር።

  13. ‘‘ሁሉም አሸባሪዎች ተገድለዋል፤ ኦፕሬሽኑም ተጠናቋል’’, ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ለኬንያ ህዝብ መልዕክት አስተላለፉ።

    ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ
    የምስሉ መግለጫ, ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ

    ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ለኬንያ ሕዝብ ባስተላለፉት መልዕክት ‘‘ሁሉም አሸባሪዎች ተደግለዋል ኦፕሬሽኑም ተጠናቋል’’ ብለዋል።

    ፕሬዚዳንቱ የ14 ሰዎች ህይወት ማለፉን እና በህንጻው ውስጥ የነበሩ 700 ሰዎችን ማውጣት መቻሉን ተናግረዋል።

  14. በርካታ ሰዎች አሁንም ህንጻው ውስጥ ይገኛሉ

    ዘመዶች የቤተሰቦቻቸውን መጨረሻ እስኪያውቁ በጭንቅ ውስጥ ቆይተዋል
    የምስሉ መግለጫ, ዘመዶች የቤተሰቦቻቸውን መጨረሻ እስኪያውቁ በጭንቅ ውስጥ ቆይተዋል

    በርካታ ሰዎች አሁንም ህንጻውን ለቅቀው መውጣት አልቻሉም። በህንጻው ውስጥ የሚገኙ ሰዎች ቁጥር በትክክል ማወቅ ባይቻልም እስካሁን ወደ 700 የሚጠጉ ሰዎች ከህንጻው ማስወጣት መቻሉን ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ገልጸዋል።

    የቤተሰብ አባላት በሆቴል ውስጥ የሚገኙ ወዳጅ ዘመዶቻቸውን ሁኔታ ለማወቅ ሆቴሉ የሚገኘበት ስፍራ ላይ ተሰባስበው ይገኛሉ።

    የህንጻው አካል ከሆቴል በተጨማሪ ቢሮዎችን በውስጡ ይዟል።

  15. ጥቃት አድራሾቹ በሲሲቲቪ ካሜራ ታዩ

    በማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ በስፋት የተሰራጨ የሲሲቲቪ ተንቀሳቃሽ ምስል ጥቃት አድራሾቹ በሆቴሉ ቅጥር ጊቢ ውስጥ ሲተኩሱ አሳይቷል።

    በሲሲቲቪ ካሜራ በተቀረጸው ተንቀሳቃሽ ምሰል ላይ ጥቁር ልብስ የለበሱ እና ከባድ መሳሪያ የታጠቁ አራት ሰዎች በህንጻው ቅጥር ግቢ ውስጥ ሲንቀሳቀሱ እና የተኩስ እሩምታ ሲከፍቱ ታይተዋል።

    የኬንያ የጸጥታ ኃይሎች የሽብር ጥቃቱ በቁጥጥር ሥር ውሏል ይበሉ እንጂ ከ30 ደቂቃዎች በፊት ከህንጻው ከፍተኛ የተኩስ እሩምታ ሲሰማ ነበረ።

    ለሽብር ጥቃቱ አልሸባብ ኃላፊነቱን እወስዳለሁ ማለቱ ይታወቃል።

  16. የናይሮቢ የሽብር ጥቃት በአሃዝ

    • 11 ኬንያውያን
    • 2 ሶማሊያውያን እና
    • 1 አሜሪካዊ መገደላቸው ተረጋግጧል።

    በጥቃቱ የቆሰሉ ሰዎች ቁጥር እስካሁን አልታወቀም።

    320 ሰዎች ከህንጻው እንዲወጡ ተደርጓል።

    ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ለኬንያ ሕዝብ መልዕክት ያስተላልፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

  17. ‘‘ለሽብር ጥቃት አንንበረከክም’’, ‘‘ለሽብር ጥቃት አንንበረከክም’’ የኬንያ የሀገር ውስጥ ደህንነት ሚንስትር

    የኬንያ የሀገር ውስጥ ደህንነት ሚንስትሩ ፍሬድ ማታይጋ እኩለ ለሊት ላይ በሰጡት መግለጫ፤ የሽብር ጥቃት የተፈጸመበትን ሆቴል ፖሊስ እንደተቆጣጠረ እና ንጹሃን ዜጎች ከህንጻው እንዲወጡ እንደተደረገ ተናግረዋል።

    ማታይጋ ይህን ይበሉ እንጂ እስከ ንጋት 12 ሰአት ድረስ ክፍተኛ የፍንዳታ እና የተኩስ ደምጽ ይሰማ ነበረ።

    ማታይጋ በቴሌቪዥን መስኮት ቀርበው ‘‘ጸጥታ አስከባሪዎች የኬንያ እና የሌሎች ሀገር ዜጎቸን ከህንጻው አስወጥተዋል። ሁኔታው በቁጥጥራችን ስር ነው። ሀገራችን ሰላም ናት። ለሽብር ጥቃት አንበረከክም’’ ብለዋል።

    የኬንያ የሃገር ውስጥ ደህንነት ሚንስትሩ ፍሬድ ማታይጋ

    የፎቶው ባለመብት, Citizen TV

    የምስሉ መግለጫ, የኬንያ የሃገር ውስጥ ደህንነት ሚንስትሩ ፍሬድ ማታይጋ
  18. የአፍሪካ ኅብረት ጥቃቱን አወገዘ

    የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማት በናይሮቢ የተከሰተውን የሽብር ጥቃት አወገዙ።

    ሊቀ መንበሩ በትዊተር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት፤ የኬንያ የጸጥታ ኃይል የወሰደውን እርምጃ አድንቀዋል።

    በኬንያ የአሜሪካ አምባሳደር የሆኑት ቦብ ጎዴክም፤ የኬንያ ጸጥታ አስከባሪዎች የወሰዱትን እርምጃ በማድነቅ መንግሥታቸው የሽብር ጥቃቱን ለመቆጣጠር ከኬንያ መንግሥት ጋር በጥምረት እየሰራ እንደሚገኝ አስታወቀዋል።

    የ X ይዘትን ይለፉት
    ይዘቱን X ይፈቅዳሉ?

    ይህ ጽሑፍ በX. የቀረበ ይዘት ይዟል። ገጹ ቴክኖሎጂዎች ወይም ኩኪዎች ሊኖረው ስለሚችል ገጹ ከመከፈቱ በፊት የእርስዎን ፍቃድ እንጠይቃለን። ፍቃድዎን ከመስጠትዎ በፊት የX ኩኪ ፖሊሲ እና የ ማንበብ ይፈልጉ ይሆናል። ይዘቱን ለማንበብ ‘እቀበላለሁ ቀጥል’ የሚለውን ይምረጡ።

    ማሳሰቢያ: በሌሎች ገጾች ላይ ላሉ ይዘቶች ቢቢሲ ኃላፊነት አይወስድም።

    የ X ይዘት መጨረሻ

  19. አል ሸባብ 47 ሰዎችን ገደልኩ አለ

    አል ሸባብ በናይሮቢ ሆቴል ባደረስኩት ጥቃት 47 ሰዎች ገድልኩ አለ።

    የአል ሸባብ ደጋፊ በሆነው ሶማሊ ሜሞ በተሰኘው ድረ-ገጽ ላይ ጽንፈኛው ቡድን ዝርዝር መረጃ ሳይሰጥ 47 ሰዎች መግደሉን ገልጿል።

    ትላንት አል ሸባብ በሆቴሉ ላይ ለደረሰው ጥቃት ኃላፊነቱን እወስዳለሁ ማለቱ ይታወሳል።

    የጽንፈኛው ቡደን ደጋፊዎችም ጥቃቱን በመደገፍ ደስታቸውን ሲገልጹ እንደነበረ ቢቢሲ ሞኒተሪንግ ዘግቧል።

    ይህ በእንዲህ እንዳለ ይፋዊ መረጃዎች እስካሁን 6 ሰዎች መሞታቸውን አረጋግጠዋል።

    ፋይል ፎቶ፡ የአል ሸባብ ታጣቂዎች ከሶማሊያ መዲና መቃዲሹ ወጣ ብሎ በሚገኝ ስፍራ እ.አ.አ. 2011 ሰልጠና ሲያካሂዱ የተነሳ ፎቶግራፍ ነው

    የፎቶው ባለመብት, AP

    የምስሉ መግለጫ, ፋይል ፎቶ፡ የአል ሸባብ ታጣቂዎች ከሶማሊያ መዲና መቃዲሹ ወጣ ብሎ በሚገኝ ስፍራ እ.አ.አ. 2011 ሰልጠና ሲያካሂዱ የተነሳ ፎቶግራፍ ነው።
  20. የዓይን እማኖች የሟቾችን ቁጥር 15 አድርሰውታል

    ይፋዊ አሃዞች እንደሚያሳዩት በዱሲት2ናይሮቢ ሆቴል ምግብ ቤት ውስጥ 5 ሰዎች መገደላቸው ተረጋግጧል። አንድ ግለሰብም ሆስፒታል ከደረሰ በኋላ ህይወቱ ማለፉ የሆስፒታል ምንጮች አረጋግጠዋል።

    ከሟቾቹ መካከል አንዱ የአሜሪካ ዜጋ መሆኑን የአሜሪካ መንግሥት አስታውቋል።

    የአስክሬን ክፍል ውስጥ የሚሰራ አንድ ግለሰብ ለሮይተርስ 15 ሰዎች መሞታቸውን አረጋግጧል።

    ትናንት 12 ሰዓት ገደማ ላይ የኬንያ የፖሊስ አባል በጥቃቱ ስፍራ ላይ
    የምስሉ መግለጫ, ትናንት 12 ሰዓት ገደማ የኬንያ የፖሊስ አባል በጥቃቱ ስፍራ ላይ