ሕንድ ከ2 ሚሊየን በላይ ሰዎች በቫይረሱ የተያዙባት ሦስተኛዋ አገር ሆነች
በሕንድ በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከ2 ሚለየን መሻገሩ ተገለፀ።
በአገሪቷ ባለፉት 24 ሰዓታት ብቻ 58 ሺህ 168 ሰዎች በቫይረሱ የተያዙ ሲሆን፤ ይህም አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን ቁጥር 2 ሚሊየን 21 ሺህ 407 አድርሶታል።
በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥርም በ20 ቀናት ውስጥ እጥፍ የሆነ ሲሆን ከፍተኛ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር በተመዘገበባቸው በአሜሪካ ወይም ብራዚል ከታየው የቫይረሱ ሥርጭት እጅግ የፈጠነ ነው ተብሏል።
በአገሪቷ ከ40 ሺህ በላይ በቫይረሱ ሳቢያ ሕይወታቸው ማለፉም ተገልጿል።
ይህም በኣለማችን ካሉ አገራት በ5ኛ ደረጃ ላይ እንድትቀመጥ አድርጓታል።
ሕንድ 1.3 ቢሊየን የሕዝብ ብዛት ያላት አገር ናት።