የእስራኤል የፍልስጤም እስላማዊ ጂሃድ ቡድን መሪዎችን መግደል እና የቡድኑ ዛቻ

የእስራኤል የፍልስጤም እስላማዊ ጂሃድ ቡድን መሪዎችን መግደል እና የቡድኑ ዛቻ

ጋዛ ውስጥ የሚገኙ የእስላማዊ ጂሃድ ታጣቂዎች ወደ እስራኤል ሮኬቶችን መተኮሳቸውን ገልጸዋል። ይህ የሆነው እስራኤል የታጣቂዎቹ የሮኬት ማስወንጨፊያዎች ላይ ጥቃት ማድረሷን ተከትሎ ነው።

የጤና ኃላፊዎች እንደሚሉት በጥቃቱ ቢያንስ ሁለት የፍልስጤም ሰላማዊ ሰዎች ተገድለዋል። በእስራኤል በኩል ሮኬቶች በአየር ላይ የመከኑ በመሆናቸው የደረሰ ጉዳት ስለመኖሩ የተባለ ነገር የለም።

እስራኤል በፈጸመችው ጥቃት ሦስት የእስላማዊ ጂሃድ አመራሮች መገደላቸው ተገልጿል።